ዳንኤልና ነፃነት (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)
ከፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም - መጋቢት 2000
በጥቅምት 1998 ዓ.ም. ላይ የሚያዝያ 1997 ዓ.ም. የህዝብ ስብሰባ እና ተከታትሎ የመጣው ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነት ያለውን ቁርጠኛ ፍላጎት አሳየ፤ ተደላድለው የነበሩ ወንበሮችን አነቃነቀ፤ በትምክህት አብጠው የነበሩትን ሁሉ ልባቸውን በፍርሃት አርበደበደው፤ ከታች መሰረት፣ ከጎን ምሰሶ፣ ከላይ ጣሪያ የሌላቸው መሆናቸውን ያለጥርጥር እንዲገነዘቡ አደረጋቸው፤ ጭካኔ ከፍርሃት ተለወደ። የፍርሃት ልጅ ያስከተለው መዘዝ ወዳጅንና ጠላትን የመለየት ችሎታችንም እስከመንሳት ደረሰ።
ቀሪውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ! (Click here to read)