ነብዩሲራክ

ትናንት እንደ ቀልድ ...
በያዝነው የፈረንጆች 2013 ዓም በወርሃ መጋቢት አጋማሽ የሳውዲ አረቢያ መንግስት " ህጋዊ ሰነድ ያልያዙትን አስወጣለሁ !" ብላ አወ ች ። ቀጠለና አፈሳ አሰሳው ተከተለ! አስፈሪው ያ ክፉ የጭንቅ ቀን በሳውዲው ንጉስ ሌላ የምህረት አዋጅ ተተክቶ ህገ ወጥ የተባሉትን ህጋዊ በሚያደርግ ህግ ተተካና የምህረቱ አዋጅ በያዝነው ህዳር መባቻ እንደሚያልቅ በተጠቆመው አዲስ የምህረት አዋጅ ተተካ !

በሂደቱ የታደሉት የተበላሸ መኖሪያ ፍቃድን ከማደስ  ምሮ አዲስ ፈቃድን አገኙ ። ያላለላቸው ከፖስፖር እድሳት መዘግየት  ምሮ አዲስ ለማውጣት ባለው ውስብስብ የኢንባሲና የቆንስል አሰራሮች ህልማቸው ሳይሰምር እዚህ ደረሱ ...ወደ ሃገር ለመግባት ፈልገው ከሃገራቸው ተወካዮች ህጋዊ ሰነድ ለማግኘት ሳይችሉ ቀሩና ተሰነካክለው ቀሩ ! በላይ በታች ብለው የመውጫ ሰነዱን ያገኙት ጥቂቶች በሰላም ወደ ሃገራቸው በሰላም ሲሸኙ የቀሩት ብዙዎች ደግሞ ሳውዲዎች እንደለመዱት ይለሳለሳሉ ብለው ከፉውን ጥቂት ቀን እቤታቸው መሽገው ሊያሳልፉ ተዘናጉ ...
አደጋውን በቅርብ የሚያዩት የመንግስታችን ተወካዮች ዜጎቻቸውን ሰብስበው መምከር ሳይችሉ ቀሩ! እንዲህ እያለ ቀን ቀንን ወልዶት የምህረቱ አዋጁ ህዳር ላይ ባባተ ማግስት ግን ዜጎች አደጋ ላይ ወደቁ ... ይህ በሁሉም ሃገር ዜጎች የመጣ ነበርና በጸጋ መቀበል የግድ ነበር ። ፍተሻ አሰሳው በመላ ሳውዲ ተጠናክሮ ሲቀጥል ቤት " ለበቤት ፍተሻ አይደረግም !" የሚል መመሪያ ወጣ ። ይህ መመሪያ ብዙዎችን አስደሰተ! ሪያድ መንፉሃ ላይ ግን መመሪያው በእኛ ዜጎች ላይ ብቻ ተጣሰ ... ህጋዊ የመንፉሃ ነዋሪዎች ሳይቀር የጥቃቱ ዳፋ ቀማሽ ሆኑ ። መንፉሃ ተሸበረች ! የሃበሻ ልጅ ቤቱ እየተሰበረ ያለ ገላጋይ በወሮበላ አረብ ወጣቶች ተቀጠቀጠ ፣ ንብረቱ ተዘረፈ ፣ ተደፈረ ! የጸጥታ ሃይሎች ቤት እየሰበሩ በመፈተሽ ወንዶችን ወደ እስር ቤት እየተለዩ ሲልኩ "ጅብ በቀደደው ውሻ ...!" እንዲሉ በፈታሾች እግር"ሸባብ " የሚባሉት ወጣት አረቦች ንብረት ከመዝረፍ  ምሮ አቅመ ደካማ ሴት እህቶችን አጠቁ! ቁጣ ተቀሰቀሰ!
ይህን ግፍ የተመለከቱ ደራሽ ገልጋይ አጥተው ተስፋ የቆረጡት ወጣት ኢትዮጵያውን ወንድሞች በአካባቢው ሳውዲዎች ዝር እንዳይሉ በማድረግ መኪናዎችን መሰባበር ያዙ! ሁከቱ ግሞ የበቀል እርምጃው በነጭ ላባሾች ተካሄደ! ጥቃቱን የአካባቢውን ነዋሪ እርምጃ ያስከፋው ነዋሪ ሻንጣውንና ቤተሰቦቹን ይዞ አደባበይ በመውጣት "ሴቶቻችን አይደፈሩ ፣ ከነቤተሰቦቻችን ወደ ሃገራችን መልሱን! " የሚል ድምጹን በአደባባይ ሲያሰማ ከጸጥታ አስከባሪዎች ጋር ወደ አላስፈላጊ ግጭት አመሩ ! ተነግሯቸው መስማት ያልቻሉት የመንግስት ተወካዮች ጣልቃ ገብተው መብት ማስከበሩ ቢቀር መሸምገል ሳይችሉ ቀረና የተፈራው ደረሰ !
ዛሬ ...በተስፋ ዛሬ ሌላ ቀን ነው! መንፉሃ ላይ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የወገን ደም ተገብሮ የሳውዲ መንግስት ህገ ወጥ ባላቸው ዜጎች ላይ የጣለው የመቶ ሽህ ብር ቅጣትና የሁለት አመት እስራት ተነሳ ! እስካሁን ባለው መረጃ 50 ሺህ የሚገመት ወገን ወደ ሃገሩ ለመግባት በማቆያ እስር ቤት እና በመጠለያ ከትሟል! የእኛ ነገር "ሰርገኛ መጠሰ በርበሬ ቀንጥሱ !" ሆነና የመንግስት ተወካዮች በስደተኛው መብት መከበር የማይተጉ ሃላፊዎችን በቅርብ ገምግመከ እርምጃ በመውሰድ የስደተኛውን ህይወት ያልደገፈው መንግስታችን ዜጎች በከፋ ችግር ማጥ ስንወድቅ አለሁላችሁ እያለን ነው ። " የምትኮሩበት ሃገር አላችሁ! ኑ በእቅፍ እንቀበላችኋለን! " ማለትም  ምሯል! አዎ! ደስ ይላል!
ዛሬ የሰሞኑ ሮሮ በረድ ብሎ ብሏል! በውጭ ሃገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም የሳውዲ መንግስት በወገኖቻቸው የደረሰውን አሰቃቂ በደል ተምልክቷልና ሰብአዊ መብት ረገጣውን ከማውገዝ ባለፈ እርዳታ እያሰባሰቡ መሆኑን መስማት ያሰደስታል! ለዚህ መሰሉ አለም አቀፍ እንቅስቃሴ ታላቅ አክብሮት አለኝ ! በሳውዲ የከተምን ከአራት መቶ ሽህ በላይ የሚንገመት የዚያች ሃገር ዜጎች አለንና ተቃውሞው በቀልን እንዳያጭር ያሳስበናል ።
ሳውዲና የእኛ ስደት ...
ሰማችን ማንቴስ ብለንና እድሜያችን ቆልለን ከደላንና ከቀናን በጠያራ ፣ አልሆን አልመች ሲል የባህር የበርሃውን ሰቆቃ ተፋጥጠን እዚህ ለደረስነው ኢትዮጵያውያን ሳውዲ አረቢያ ባለውለታችን ናት ! በአብዛኛው በሳውዲ አሰሪዎችና በአንዳንድ የመንግስት ተቋማት ሰራተኞች የሚደርስብንን የመብት ጥሰት ችለን ላለፍን ሰላማዊ ነዋሪዎች "በሰብአዊ መብት ጥሰት የምትወነ ለው አረባዊቷ  ገር ከ ገራችን የተሻለች ናት! " እስከ ማለት መድረሳችን እውነት ነው ። ስለ እውነት እንነጋገር ከተባለና የሰብአዊ መብቱን ነገር ችላ ብለን ራስን መደገፉ ካመራን ሳውዲ አረቢያ ራሳችን ጠቅመን ቤተሰቦቻችን መጥቀም የቻልንባት ሁለተኛ ሃገራችንናት ብል ማጋነን አይቦንም ። ይሁንና ይህች የምናመሰግናት ሃገር አልፎ አልፎ ከምታወጣው ህግ ጋር በተገናኘ የእኛን መብት የሚያስከብርልን ጠንካራ ተወካይ አጥተን ህግ እየተጣሰ ተጎድተናል። ይህ ብቻ አይደለም በግርድፉ እናውራው ካልን ህግና ስርአትን ተከትለው የማይኖሩ ወገኖች በሚሰሩት ህገነወጥ ስራ በሚሰጠን ስም ገጽታችን ከመጉደፉ አልፎ ተርፎን "ለሃጥአን የመጣው ለጻድቃን !" እንደሚባለው የሃጥአኑ ጥቃት ለቀረው ሰላማዊ ነዋሪ ሲተርፈው የመንግስት ተወካዮቻችን ዋቢ አልቆምልን እያሉ ኑሯችን ከፍቷል ። ካለን የገቢ ምንጭ አንጻር አኗኗራችን በህብረት መሆኑም ጎድቶናል። ይህ ከጥቂቱ ጉዳት መካካል ጥቂቱ ቢሆንም ኑሯችን ካከፋው ምክንያትነት ቀዳሚ ለመሆኑ ጥርጥር የለኝም! ከዚህ አንጻር በሰሞኑ አሰሳና ፍተሻ በላቡ ከሚያድረው ጎልማሳ እና ጉብሏ  ምሮ አባወራው ሆነ የቤት እመቤቷ ህገ ወጥ ተብለን እንደወጣን ልንቀር የምንችልበት አደጋ ተደቅኖብናል። ዜጎች በከባድ ውጣ ወረድ ለአመታት ያፈራነው  ብት ቀርቶ የአብራክ ከፋይ ልጆች ቤተሰቦቻቸውን ሳይሰናበቱ ከ ገር ለሚባረሩበት አካሄድ በምክክር መላ ካልተበ ለት አሰፈሪና አስደንጋጭ ነው !
የወገን ቁጭትና ቁጣ እና ቁጣው የደረሰው የሳውዲ መንግስት ...
በመንፉሃን የተፈጸመብንን ቅጥ ያጣ ጥቃት ተከትሎ ግፍ በደል መከራውን በዘመንኛው የመረጃ መረብ ሲናኝ ሃዘናችን የተጋራው ከሃገር ቤት  ምሮ በመላ አለም ከጫፍ እስከ ጫፍ በቁጣ የተነሳው የኢትዮጵያን ቁጣ መልዕክት ለሳውዲዎች ደርሷቸዋል። ወደ ቀጠለው አለም አቀፍ ከጅምሩ ሳውዲን ከአልቃኢዳ ጋር በመወን ል የተ መረው አስፈሪ የነበረ ቢሆንም በቀጣይ ሰልፎች ጥያቄው ሰብአዊ መብትን አክብሩ በሚል መሻሻሉ ለሳውዲ ንጉሳዊ ቤተሰቦች እያስተላለፈ ያለው መልዕክት ቀላል አይደለም ባይ ነኝ ። በዋሽንግተኑ የመ መሪያ ተቃውሞ የተሰማው ሳውዲን ከአልቃኢዳ ጋር አጎዳኝቶ የመወንጅል እና ከበቂ ማነስ የተነሳ የብዙሃን ሙስሊማንን መመሪያ የቁርአን መልዕክት በነጭ ቀለም የተጻፈበትን ደማቅ አረንጓው የሳውዲ አረቢያ ባንዴራን ወደ ማንቋሸሽ እንዳያመረ የነበረን ስጋት መወገዱ ያስደስታል ። ይህም ብዙ የሳውዲ ነዋሪዎችን አስደስቶናል! ለተፈጸመው ግፍ ማካካሻ ባይሆንም በመጠለያዎች የምንሰማው የሰቆቃ ጩኸት ረገብ ብሏል። የሳውዲ መንግስት በመጠለያ ያሉትን ዜጎች መጠለያ ሲታይ የሰነበተውን የምግብ ፣ የውሃ እና የህክምና አቅርቦት እያስተካከለው መገኘቱን ከመጠለያው ከሚገኙ ግፉአን ማረጋገጥ ችያለሁ ። በቀን አንድ ሚሊዮን ብር የሚደርስ ወጭን የሳውዲ መንግስት ፣ ከማውጣት  ምሮ ወደ ሃገር ቤት መግባት የሚፈልጉ ኢትዮጵያውንን ለማሰባሰብ 300 ያህል አውቶቡሶች በሪያድ በመካ ተመድበው የማጓጓዙን ሂደት ከ መሩ ቀናት ተቆጥረዋል። ወጭውን ይሸፍነዋል ተብሎ ከተነገረኝ ከኢትዮጵያ አየር መንገዳችን ወደ ሃገር ቤት የማጓጓዙ ዘመቻ ጎን ለጎን የሳውዲ መንግስት በሳውዲ አየር መንገድ በኩል ነጻ የማጓጓዝ ስራ በመካሄድ ላይ መሆኑን መረጃዎች ደርሰውኛል ።
መልካሙ ጅምር ፣ ሰው ሃይልና የመረጃው እጥረት...
ከላይ ለመጠቆም እንደሞከርኩት በሪያድና በመካ ስደተኛን የመቀበሉ ስራ እየተሰራ ቢሆንም በማቆያው ባለው የስደተኛ ብዛት አንጻር በጅዳ ወደ ሃገር መግባት የሚፈልጉትን ወደ ማረፊያ የማጓጓዙም ሆነ ባሉበት የመመዝገቡ እንቅቃሴ በጅዳ ገና አልተ መረም ። በጅዳ የሽሜሲማረፊያ እስር ቤትና በሪያድ መጠለያ ያለውን ምዝገባ እና የመጓጓዣ ሰነድ አቅርቦት ለማሳለጥ የኢትዮጵያ መንግስት ልዑክ እና ድጋፍ የሚሰጡ ሃላፊዎችን አሰማርቶ ስራው እየተሰራ ቢሆንም ከፍተኛ ቁጥር ላለው ዜጋ ግልጋሎት ለመስጠት የሰው ሃይል እጥረት መስተዋሉ አልቀረም። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነን በቅርቡ ለቀናት ዝግ የነበረውን የጅዳ ቆንስል አመዘጋት መጥቀስ ይቻላል። ምንም እንኳን ቆንስል መስሪያ ቤቱ ስራውን ለቀናት የዘጋበትን ምክንያት በግልጽ ባወጣው ማስታወቂያ አልተገለጸም ። ምክንያቱ ባልተገለጸው የጅዳ ቆንስል መዘጋት ብዙዎችን አስቆጥቷል " የታመመ ቢሞት እንዴት እንቅበር? ፖስፖር ለማሳደስ ፣ የታደስ ለመቀበል ፣ ሰነድ ማስተካከል ቢያስፈልግ ፣ የጋብቻ ወረቀት ማረጋገጫና እና ተመሳሳይ ግልጋሎት ስንፈልግ የት እንሂድ? " ሲሉ በማጠየቅ በአስቸኳይ ቆንስሉ እንዲከፈት ነዋሪዎች መንግስትን ተማጽነዋል። የቆንስሉን መዘጋት ምክንያት ሃላፊዎችን ጠይቀን መላሽ ብናጣም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩም ቶዌድሮስ አድሃኖም "የጅዳ ቆንስል አገልግሎት እንዳይሰጥ የተዘጋው የቆንስላው ሰራተኞች ስደተኞቹን ወደ  ገራቸው ለመመለስ እንዲያግዙ ስለተፈለገ ነው " ብለው በትዊተር መረጃ አቀብለውናል። ይህ የሚያሳየው የሰው ሃይል እና የመረጃ ልውውጥ እጥረት መሆኑን ለመረዳት መማር መመራመርን አይጠይቅም። ይህ እውነታ ፈጦ እያለ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ግልጋሎት ለመስጠት ፈቃደኛ የሆኑትን የኮሚኒቱ መስሪያ ቤትና ችግሩ ችግራችን ነው በሚል መክረውና ዘክረው አቤቱታ ያቀረቡ ወገኖችን ለመቀበል
አልደፈሩም። ምክንያቱን የሚያውቁት ሃላፊው ቢሆኑም ሲሆን ነዋሪውን አስቸኳይ ሰብሰባ ጠርተው ፣ ያ ቢገድ የድጋፍ ጥያቄውን በበጎ ተመልክተው አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ አለመቻላቸው ሂደቱን ከመሳለጥ እንዳይገታው ስጋት አለ። ሌላው በሪያድና በጅዳ ሃላፊዎች ዙሪያ የሚታየው የመረጃ ክፍተት የግልጋሎት አሰጣጡን አልፎ አልፎ የሚስተዋለውን የመብት ገሰሳ ከቁጥጥር ውጭ እንዳያወጣው ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ለዚህም በሪያድ መንፉሃና በተለያዩ አካባቢዎች ፣ በጅዳና በመካ "ወደ ሃገራችን ውሰዱን ?" በሚሉ ዜጎች እና በመንግስት ጸጥታ አስከባሪዎች መካከል የሚፈጠሩ ፍጥጫና ግጭቶችን በመንፉሃ የታየውን አደጋ እንዳይደግመው ለመከላከል ይረዳል። በመንፉሃ ባየነው የተንቀሳቃሽ ምስል ባየነው ድብደባና ውክቢያ አድራሻቸው የጠፋ ወገኖች በፖሊስ ጣቢያዎች፣ በሆስፒታልና በመጠለያው ፈልገው ያጧቸውን ወገኖቻቸውን በሚመለከት መረጃ ለመስጠት ፈልገው ወደ መንግስት ሃላፊዎች ቢደውሉም ምላሽ እንዳላገኙ በምሬት የገለጹልኝ በርካታ ናቸው ። በውክበቱ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች የትየለሌ የመሆናቸውን ያህል የደረሱበት የማይታወቅ ዜጉች ጉዳይ ከሚሰራው የማጓጓዝ ስራ በተጓዳኝ በመረጃ ልውውጥ ተደግፎ መሰራት ያለበት ስራ ነው ። ይህንና ይህን መሰል ጉዳዮችን ስንመለከት በመንግስት ሃላፊዎች የመረጃ ተቀባይ አለመኖር ነገ ቢያንስ ለህሊናችን ተወቃሽ እንዳያደርገን ዛሬ መሰራት ያለበት ስራ ነው ባይ ነኝ። ከዚህ አንጻር መረጃ ትልቅ አስተዋጽጾ እንዳለው በቦታው የሚገኙ የመንግስት ተወካዮች ሊያጤኑት ይገባል። ይህን ክፍተት ለመዝጋትም የአደጋ ጊዜ ተጠሪና መረጃ ተቀብሎ የሚያጣራ ኮሚቴ በአፋጣኝ ሊቋቋም ይገባል። የኮሚቴው አባላትም ነዋሪውን ሃያ አራት ሰአት ክፍት የሆነ ነዋሪውን የሚያስተናግዱበት ስልክ ሳይውል ሳያድር መሰራት ካለበት ስራ አንዱ መሆኑን ማጤን ብልህነት መሆኑን ጠቁሜ የማለዳ ወጌን ልቋጨው ወደድኩ...


እስኪ ቸር ያሰማን!

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ