ፍትህን ፍለጋ፣ ዳኝነት አሰሳ (አባኪያ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

የአባኪያ ማስታወሻ፤ አባኪያ ተመልሷል**

ትናንት ለጠበቆቻችን፣ ዛሬ ደግሞ ለዳኞቻችን

“ፍትህን ፍለጋ፣ ፍትህን አሰሳ”

“ፍትህን ፍለጋ፣ ፍትህን አሰሳ” የሚቀጥለው የቴዲ አፍሮ ዘፈን አልበም መጠሪያ ይመስለኛል። “ቃሊቲ ቃሊቲ” ሊለውም ይችላል። መቼም ዶ/ር ብርሃኑ ወይም ኢንጂነር ኃይሉ ወይንም ብርቱካን ሚደቅሳ ቢዘፍኑ አያምርባቸውም። ነገር ሁሉ ለበጎ ነው የሚለውን የሐዋርያውን ቃል ካመንበት፤ ምናልባትም የቴዲ አፍሮ መታሰር ለበጎ ነው። ከዚህ ቀደም ጽሑፌን ያቆምኩበትን አልዘነጋሁም። ወደዚያ እመለሳለሁ። ለጊዜው ግን ፈተና ላይ ከርሜ ጠፋሁኝ። ኢትዮጵያ የተውኩትን/ያቋረጥኩትን ትምህርት እዚህ ቀጥያለሁ። ይሄ የጀመርኩትን ትምህርት ምዕራብና ምስራቅ ጫፍ ካላቸው፣ ከምዕራብ ጫፍ ምስራቅ ጫፍ የመሄድ ያህል ዞሬ ነው የጀመርኩት። መቶ ሰማኒያ ዲግሪ መዞር የሚሉት አይነት ነገር። ቀድሞ እማር የነበረው የcivil law ሥርዓትን መሰረት ያደረገውን የኢትዮጵያን ሕግ ነበር። አሁን ወደ common law ዞሬያለሁ። ሕግን - ሕግ ከሚከበርበት ሀገር ስትማሩት እንዴት ደስ ይላል መሰላችሁ። አሁን የምማረው በተለይ እንግሊዝ፣ ካናዳ፣ አውስትራሊያ፣ አሜሪካና ካናዳ የሚከተሉት የሕግ ሥርዓት ቀደም ሲል ምናልባትም ከአንድ ሺህ ዓመታትም በፊት ጀምሮ የተወሰኑ ውሳኔዎችን መሰረት ያደረጉ፣ መርሆዎችና ሕግጋት በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ለሚፈጠርና ለሚገኝ ጉዳይ በተመሳሳይ መልኩ የሚወሰኑበት የሕግ ሥርዓት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እኛ እና ፌሽት (ያሬድ ክንፈ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ያሬድ ክንፈ ከስዊድን (ሀገር ቤት ላለ ወዳጅ የተጣፈ) ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

Teddi on stage in Stockholmጌትዬ! ከነመላው ቤተሰብህ መልካም የገና በዓል ይሆንልህ ዘንድ ከልቤ እመኛለሁ!

 

እዚህ ስዊድን ውስጥ የኢትዮጵያን ገና ምክንያት በማድረግ ቅዳሜ ታህሳስ 19 ቀን 2000 ዓ.ም. (ዲሴምበር 29 ቀን 2007 ዓ.ም.) ፌሽታ ተደርጎ ነበር። ዋና ከተማዋ ስቶክሆልም ውስጥ ሊልሆልመን እተባለው ክፍለከተማ በኢድሮትስሐለን አዳራሽ ውስጥ ከምሽቱ አራት ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ (ለእሁድ አጥቢያ) 10 ሰዓት ድረስ ነበር ዝግጅቱ። መድረኩን ተቆጣጥሮት የነበረው ተወዳጁ ቴዲ አፍሮ (ቴድሮስ ካሣሁን) ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወደምዕራብ በሄድን ቁጥር ራዕያችንን እናጣለን

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ወደምዕራብ በሄድን ቁጥር ራዕያችንን እናጣለን

ማስታወሻ ከሰሜን አሜሪካ

ችግርና ምሬት እንደ መነሻ - አንደኛ

“በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ሀሳብህ አርፎ ከሆነ ብዙ ሥራ ይጠብቅሀል” ይላል ከሁለት ሣምንት በፊት የደረሰኝና በየቀኑ እንደዳዊት የምደግመው የምስኪኑ ጓደኛዬ ደብዳቤ። በጽሁፍና በድርሰት ታሪክ ውስጥ በዚህች አጭር ሕይወቴ እንደተረዳሁት ምሬትንና ችግርን እንደመጻፍ የሚቀል ዓለማቀፋዊ ነገር የለም። ለመጻፍም ለመናገርም የሚቀል ርዕስ - ችግር ነው። ባለጸጋዎቹም፣ ነዳያኑም አገራት የችግራቸው ዝርዝር ተዝቆ አያልቅም። አሁን ካናዳና አውስትራሊያ ችግር ያለባቸው ይመስላሉ? እንደውም እነዚህ ሰዎች ሥልጣኔን ብቻ ሳይሆን ችግርንም ነው እንዴ የሠሩት? እስክትሉ ድረስ ችግር ቤቱን የሠራበት ምድር እዚህ ነው። እንዲሁም ዜናዎቻቸውን ብትሰሙ፣ የሚጻፉትም የሚነገሩትም ምሬትና ችግር ይበዛባቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...