ፍትህን ፍለጋ፣ ዳኝነት አሰሳ (አባኪያ)
የአባኪያ ማስታወሻ፤ አባኪያ ተመልሷል**
ትናንት ለጠበቆቻችን፣ ዛሬ ደግሞ ለዳኞቻችን
“ፍትህን ፍለጋ፣ ፍትህን አሰሳ”“ፍትህን ፍለጋ፣ ፍትህን አሰሳ” የሚቀጥለው የቴዲ አፍሮ ዘፈን አልበም መጠሪያ ይመስለኛል። “ቃሊቲ ቃሊቲ” ሊለውም ይችላል። መቼም ዶ/ር ብርሃኑ ወይም ኢንጂነር ኃይሉ ወይንም ብርቱካን ሚደቅሳ ቢዘፍኑ አያምርባቸውም። ነገር ሁሉ ለበጎ ነው የሚለውን የሐዋርያውን ቃል ካመንበት፤ ምናልባትም የቴዲ አፍሮ መታሰር ለበጎ ነው። ከዚህ ቀደም ጽሑፌን ያቆምኩበትን አልዘነጋሁም። ወደዚያ እመለሳለሁ። ለጊዜው ግን ፈተና ላይ ከርሜ ጠፋሁኝ። ኢትዮጵያ የተውኩትን/ያቋረጥኩትን ትምህርት እዚህ ቀጥያለሁ። ይሄ የጀመርኩትን ትምህርት ምዕራብና ምስራቅ ጫፍ ካላቸው፣ ከምዕራብ ጫፍ ምስራቅ ጫፍ የመሄድ ያህል ዞሬ ነው የጀመርኩት። መቶ ሰማኒያ ዲግሪ መዞር የሚሉት አይነት ነገር። ቀድሞ እማር የነበረው የcivil law ሥርዓትን መሰረት ያደረገውን የኢትዮጵያን ሕግ ነበር። አሁን ወደ common law ዞሬያለሁ። ሕግን - ሕግ ከሚከበርበት ሀገር ስትማሩት እንዴት ደስ ይላል መሰላችሁ። አሁን የምማረው በተለይ እንግሊዝ፣ ካናዳ፣ አውስትራሊያ፣ አሜሪካና ካናዳ የሚከተሉት የሕግ ሥርዓት ቀደም ሲል ምናልባትም ከአንድ ሺህ ዓመታትም በፊት ጀምሮ የተወሰኑ ውሳኔዎችን መሰረት ያደረጉ፣ መርሆዎችና ሕግጋት በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ለሚፈጠርና ለሚገኝ ጉዳይ በተመሳሳይ መልኩ የሚወሰኑበት የሕግ ሥርዓት ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...