የበጎው ሰው፣ የጎልማሳው ህልፈት (የማለዳ ወግ)

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ነቢዩ ሲራክ

"... በሕብረት መኖር አለብን ብሎ የሚመክር የሚዘክር ድንቅ ሰው ነበር፣ አቡኬ"

Abukee Alex, አቡኬ አሌክስ

በያዝነው ሣምንት ... በአብዛኛው የሐበሻ መገናኛ መንደር፣ በማኅበራዊ ድረ ገጽ ዋንኛ መድረክ በFacebook መስኮት አንድ መሪር መርዶ ተሰምቷል። የትሁት፣ አስተዋይና አርቆ አስተዋዩ በጎ ሰው፣ የጎልማሳው የአቡኬ አሌክስ ህልፈት። የአቡኬ አሌክስ በድንገት መለየት ጥልቅ ኀዘናን ሁላችንንም አንገብግቦናል። "ከሞቱ አሟሟቱ" እንዲሉ አቡኬ ባንድ ጀንበር ታይቶ በርቶ፣ ባንዱ ጀንበር ሳይታሰብ ጠፍቶብናል። እናም በቅርብ ከሚያውቁት፣ ቤተሰብ ዘመድ አዝማድ ጓደኞች እኩል በሥራው በዝና የምናውቀው በኀዘኑ አዝነን ከፍቶናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግንቦት ፖለቲካ

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ተስፋዬ ገብረአብ

በዚህ በወርሃ ግንቦት ከጥቂት በላይ ጆሮ የሚጎትቱ ዜናዎች መስማታችን አልቀረም። የኦሮሚያ አመፅ በገጠር ከተሞች መቀጠሉ፣ የቦሌ አለማቀፍ አይሮፕላን ጣቢያን ስም ለመቀየር መታሰቡ፣ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም የስራ ፍለጋ ማመልከቻ ማስገባቱ፣ የህወሃት የፀጥታው መስሪያ ቤት ባልደረቦች በውስጥ ሽኩቻ መናጣቸው፣በርካታ የስርአቱ ደጋፊዎችና ቤተሰቦቻቸው ባለመረጋጋት ስሜት የሽሽት ጉዞ መጀመራቸው፣ የኦሮሞ የፖለቲካ ድርጅቶች ተባብረው የኢትዮጵያን መንበረ ስልጣን እንዲረከቡ ግፊት በመደረግ ላይ መሆኑ እና ሌሎችም በወርሃ ግንቦት ከተሰሙ አበይት ዜናዎች መካከል ናቸው። አንዳንዶቹን ርእሰ ጉዳዮች በጨረፍታም ቢሆን ፈታ አድርጎ ማየቱ አስፈላጊ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በደመነፍስ የሚነዱ ትራፊክ ፖሊሶችና የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ችግር

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ዩሱፍ ከዲ

AA traffic police. በደመነፍስ የሚነዱ ትራፊክ ፖሊሶችና የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ችግር

የቅዳሜ ሚያዝያ 1 2008 አጭር ገጠመኝ

ከሜክሲኮ በባልቻ አድርጎ በአብነት ወደ አውቶቡስ ተራ የሚወስደውን በተለምዶ ዶልፊን የሚባለውን ታክሲ ስሳፈር፣ ሰዓቱ ገና አንድ ሰዓት ከሃያ አካባቢ ነበር። ታክሲውም አንድ ወይም ሁለት ሰው ቀርቶት ባልሞላበት ሁኔታም ነበር መንቀሳቀስ የጀመረው። ይህ ድርጊቱ የሾፌሩን "ለሰዓት/ለጊዜ እንዲሁም ለጫናቸው ተሳፋሪዎቹ ያለውን አክብሮት" ያሳየኝ ሆኖ አግኝቼዋለሁና እንዳከበርከን ክበር እያልኩኝ በውስጤ መልካም እየተመኘሁለት ነው የተጓዝኩት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዲያቆን ሙት!

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

አሊ ጓንጉል

Daniel Kibret. ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

ይህ ጽሁፍ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በቅርቡ ‘“ሀገር ማለት ሰው ነው”! እስቲ ሙት በለኝ!’ ሲል ለለቀቀው ጽሁፍ መልስ ነው። ... እስካሁን ድረስ “ሀገር ማለት ሰው ነው” የሚባል ዘፈን መኖሩን ሰምቼም አይቼም አላውቅም። በዚህ ስም የሚጠራ ዘፈን ኖሮ እኔ ያላወቅሁ እንኳን ቢሆንም፣ “ሀገር ማለት ሰው መሆኑን” ሊያስክድ የሚችል አንዳችም ነገር ያለ አይመስለኝም። በዚህ ስም የሚጠራ ዘፈን ጨርሶ ሳይኖር፣ የበድሉ ዋቅጅራን “ሀገር ማለት የኔ ልጅ ... ሰው ነው ...” በሚል ርዕስ የሚታወቀውን ታላቅ ግጥም እንዲሁ “ዘፈን” በማለት ለመተቸት ወይም ለማውረድ ከሆነ ደግሞ፣ ዲያቆኑን የባሰ የታሪክ፣ የኃይማኖት እና ከሁሉም በላይ የስነ-ጽሁፍ ድህነቱን ይናገርበት ይመስለኛል። ምክንያቱም ሀገር ማለት ሰው ነው! ላስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ሀገር ማለት ሰው ነው”፤ እስኪ ሙት በለኝ!

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ዳንኤል ክብረት

ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገርሙኝ ዘፈኖች አንዱ “ሀገር ማለት ሰው ነው” የሚለው ነው። እሥራኤላዊና ጂፕሲ ይህንን ቢሰሙ ምን ይሉ ይሆን? እላለሁ። አይሁድ በመላው ዓለም ለ1900 ዓመታት ያህል ተበታትነው ሲኖሩ በየአካባቢው ሰው ነበራቸው፤ያውም እንደ ብረት የጠነከረ ማኅበረሰብ፤ ሀገር ግን አልነበራቸውም። ሀገር ማለት ሰው ከሆነ አይሁድ ሀገር ፍለጋ ከሺ ዓመታት በላይ መኳተን አልነበረባቸውም። በአውሮፓ የሚኖሩት ጂፕሲዎች የታወቀ ማኅበረሰብ አላቸው። ነገር ግን ሀገር የላቸውም። ሀገር ማለት ሰው ቢሆን ኖሮ ጂፕሲ የሚባል ሕዝብ ብቻ ሳይሆን ጂፕሲ የሚባል ሀገርም ይኖር ነበር። ግን የለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የልጄን ነገር አደራ! እባክህ ነፍሴን አሳርፋት" እናት ሎሜ ረጋስ

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

የማለዳ ወግ ...

* በኀዘን የሚላወስ እንስፍስፍ የእናት አንጀት

* የኮንትራት ሠራተኛዋን እህት ቤዛን አፋልጉኝ!

ነቢዩ ሲራክ

ሆዴን ያላወሰው የእማማ ሎሜ አደራ

Beza Ashenafi Engida and her mother Lome Regass. እህት ቤዛ አሸናፊ እንግዳ እና እናት ሎሜ ረጋስ

የእናትን መሪር ኀዘን ሰምቼ ሆዴ ተላውሷል፣ የእናትን ጥልቅ ጭንቀቷ፣ ያለ አባት በአሳር በመከራ ያሳደገቻት የእናትን ሎሜ መሪር ኀዘን ተረድቼ ሕመም መታመሜ እውነት ሳለ፤ በዝምታ እየቆሰልኩ ማስረጃና መረጃ ፍለጋ መዋተቴ ሕመሜን አክብዶታል። ከጉያዋ ወሽቃ፣ በትንፋሿ አሙቃ፣ ስታገኝ በደስታ፣ ስታጣ ተከፍታ፣ ድሃ አደግ ቤቷን አሟሙቃ፣ ነገ ልጆቿን ለወግ ለማዕረግ የማድረስ ምኞት ተስፋን ሰንቃ፤ ተስፋዋን የተነጠቀች እናት እንባ ውስጤን አድምቶ አቃጥሎታል። እናት ዛሬ ማለዳ በላኩልኝ መልዕክት እንዲህ ይላል “የልጄን ነገር አደራ! እባክህ ነፍሴን አሳርፋት" …

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ