የሥልጣኔ ሞት - ከድርሰት ሞት
ዳንኤል ክብረት
የዛሬ 600 ዓመት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የተባለ ኢትዮጵያዊ ደራሲ "አርጋኖን" የተሰኘ መጽሐፍ ይደርሳል። ይህንን መጽሐፍ የተመለከቱ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንትም እጅግ ያደንቁና ለንጉሡ ለዐፄ ዳዊት ያቀርባሉ። ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም መጽሐፉን ተመልክተው በማድነቅ በወርቅ ቀለም እንዲጻፍ አዘዙ። አባ ጊዮርጊስንም ሸለሙ።
የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
ዳንኤል ክብረት
የዛሬ 600 ዓመት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የተባለ ኢትዮጵያዊ ደራሲ "አርጋኖን" የተሰኘ መጽሐፍ ይደርሳል። ይህንን መጽሐፍ የተመለከቱ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንትም እጅግ ያደንቁና ለንጉሡ ለዐፄ ዳዊት ያቀርባሉ። ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም መጽሐፉን ተመልክተው በማድነቅ በወርቅ ቀለም እንዲጻፍ አዘዙ። አባ ጊዮርጊስንም ሸለሙ።
መጽሐፍ፦ ወሬ ነጋሪ
ደራሲ፦ መሐመድ ይማም
ግምገማ፦ በልጅግ ዓሊ
በሚያዚያ ወር የሰሜን አሜሪካ ክረምት ገና ሙሉ በሙሉ ሳይለቅ በፊላደልፊያ ከተማ ውስጥ በማይታወቅ ሰው ኢትዮጵያዊቷ ጀግና ተገደለች። በምሳ ሰዓት አካባቢ ወደ ቤት የተመለሰችው እህቷ ጠዋት በሰላም የተለየቻትን በደም አበላ ውስጥ ተዘፍቃ አገኘቻት። ፖሊስም ጠራች። የፍላደልፊያ ፖሊስ ይህንን የተቀነባበረ ግድያ የፈጸመውን ወንጀለኛ መያዝ ስላቃተው እንቆቅልሹ ያልተፈታ በሚል መዝገቡን ዘጋ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
ዳንኤል አበራ
ሰሞኑን የአንድ መጽሐፍ "የስደተኛው ማስታወሻ" ቅጅ በድረ መረብ ከመሰራጨቱ በፊት እና በኋላ አነጋጋሪ ሆኗል። ከጸሀፊው ተስፋዬ ገብረአብ ስብእና ጋር ተዳምሮ በመጽሐፉ ውስጥ የታጀሉት ጽሁፋዊ፣ ታሪካዊ፣ ሃይማኖታዊ እናም ሌሎች ግድፈቶች አንድም ይሁነኝ ተብሎ ለአንድ ግብ በመሰራቱ፤ አንድም ባለማወቅ በመደረጉ ለአማርኛ ጽሁፍ አንባቢያን እነዚሀን ነቅሶ ማሳየቱ አግባብ ሆኖ ታይቶኛል። በዚህ እና በቀጣይ ጽሁፎቼ እነዚህን ቋንቋ እና ጽሁፍ ተኮር ግድፈቶች አሳያለሁ።
የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
ዳንኤል ክብረት
ባለፈው ሳምንት ተስፋዬ ገብረ አብ አቡነ ተክለኃይማኖትን በተመለከተ ያነሣቸውን ነጥቦች ማየት ጀምረን 'የሦስቱን ተክለ ሃይማኖቶች' ጉዳይ ለዛሬ አቆይተነው ነበር። እንቀጥል።
1) የሰባተኛው መክዘ ተክለኃይማኖት
ተስፋዬ የጠቀሳቸው የሰባተኛው መክዘ ተክለኃይማኖት የሉም። እስካሁንም እንደርሱ ፈጠራቸውን የሚናገሩ እንጂ ማስረጃ ያመጡ አልተገኙም።
የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
ዳንኤል ክብረት
ተስፋዬ ገብረአብ "የስደተኛው ማስታወሻ" የተሰኘ መጽሐፍ ማውጣቱንና ባነበው መልካም እንደሆነ ገልጦ አንድ ወዳጄ "ስስ ቅጅውን" ከሀገረ አሜሪካ ላከልኝ። ከዚህ በፊት ሌሎች መጻሕፍቱን አንብቤያቸዋለሁ፤ በአጻጻፍ ችሎታው የምደሰተውን ያህል እንደ አበሻ መድኃኒት ነገሩን ሁሉ እርሱ ብቻ የሚያውቀው ምስጢር ስለሚያደርገው፤ በአንዳንድ ጉዳዮችም ሆን ብሎም ሊያናጋቸው የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ እሴቶች ያሉ ስለሚመስለኝ፤ ተስፋዬ ለምን እንደዚህ ይጽፋል? እያልኩ የምጠይቃቸው ነገሮች ነበሩ።