የስየ “ምስጢሮች”

“Freedom & Justice in Ethiopia” - By Siye Abrahaተስፋዬ ገብረአብ

ስየ አብርሃ የፃፈውን መጽሐፍ አነበብኩት።

የተደጋገመውን ዝባዝንኬ እየዘለልኩ እንደምንም ጨረስኩት። የስየ ወንድሞች የገዟቸው መኪኖች የሻንሲ ቁጥር ምንም ስለማያደርግልኝ እየነጠርኩ አልፌዋለሁ።

ስየ ላይ አልፈረድኩበትም። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሚገማሸረው ብዕር (ያገር ልጅ)

Tesfaye Gebreab, ተስፋዬ ገብረአብያገር ልጅ

ስለተስፋዬ ገብረአብ ሸጋ የአማርኛ ቋንቋ ብዕርተኝነት እንዳዲስ እዚህ ላይ አላነሳም። በጣም ብዙ ብዙ ተቺዎችና አስተያየት አንጓቾች በቁጥራቸው መጠን ብለውታል። ደራሲው ተስፋዬና የፕሮፓጋንዳ መጣጥፍ ጣፊው ተስፋዬም የብዕር ውበት ለዛቸው አንድ ነው። ልዩነታቸው ከዘላቂው የፈጠራ ሥነ-ጽሑፍ ሰብዕናና ካላፊው ከረጋፊው የፕሮፓጋንዳ ሰውነት ላይ ብቻ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ከሀገር በስተጀርባ” (ገሠሠ እንግዳ)

ከሀገር በስተጀርባገሠሠ እንግዳ

በኢትዮጵያ በህይወቴ ዘመን ሦስቱን ሥርዓቶች ማለት የዓፄ ኃይለሥላሴ፣ የኰለኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም እና የመለስ ዜናዊ መንግሥታት መልካቸው ብቻ ሳይሆን ተግባራቸውንም ጭምር ለማስተዋል ከበቁት ሰዎች ውስጥ አንዱ ነኝ። በተለይም በሀገራችን ለውጥ ለማምጣት “ዳቦ ለተራበ”፣ ”መሬት ላራሹ” የሚል ህያው መፈክር ይዞው “አትነሳም ወይ የግፍ አገዛዝ አይበቃህም ወይ?!” እያሉ በአደባባይ ወጥተው ይጮኹ ከነበሩት ተማሪዎች አንዱ ሁኘ ብዙ ውጣ ውረድ አልፈው እዚህ ከደረሱት ትውልድ አንዱ ነኝ። የወጣቱ አስራት አብርሃምን መጽሐፍ ሳነብ የቀሰቀሰብኝ ትዝታም ያ ያሳለፍኩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች እንቅስቃሴ የእሳትነት ዘመኔ ነበር። ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ነፃነትና ዳኝነት በኢትዮጵያ” - በስየ አብርሃ

“Freedom & Justice in Ethiopia” - By Siye Abrahaእንደ ግምገማ - ኩችዬ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

“መጽሐፍ!” ሲሉት ሰፍ የሚል ከራማ ቢጤ አለብኝ መሰል ስየ አብርሃ ደረሱ የተባለው መድብል እጄ እስኪገባ ቸኩዬ ነበር። ባገራችን የቅርብ ዘመን ታሪክ ላይ አሻራቸውን ካተሙት ጥቂት ስዎች መሀል ናቸውና እኒህ ሰው የሚሉትን ለማወቅ ብተጋ አይፈረድኝም። ጀመርሁ የሚሉት የሁለተኛው ምዕራፍ ጉዟቸው የምንፈልገው ዓይነት መሆኑን የሚያመላክቱ ፍንጮች ያዘለ ሊሆን ስለሚችልም መጽሐፉን ለማንበብ በቂ ምክንያት ያለ መሰለኝ። ላወቀበት በመስመሮቹ መሀል የተሰነጉትን ሁሉ መመርመር ነው።  ሙሉውን አስነብበኝ ...

ተስፋዬ ገብረአብ እና ሁለቱ ዝሆኖች

Yederasiw Mastawesha, የደራሲው ማስታወሻእጅጋየሁ አወቀ

”... ደራሲ ተስፋዬ ራሴን ነፃ አውጥቻለሁ የሚሉትን የቀድሞ የፖለቲካ ድርጅታቸውን በመደገፍ ተቃዋሚውን፤ በተለይም በአሰብ ጉዳይ ላይ ከመለስ የተለየ አቋም የወሰዱትን ቢታገሉ፤ እየሠሩ ያሉት ”ሀገሬ” ለሚሏት ለኢትዮጵያ ወይስ ለእናታ ሀገራቸው ለኤርትራ? ልብ በሉ፣ በአሰብ ላይና የአልጀርሱን ስምምነትና የሔጉን ውሳኔ ውድቅ እናደርጋለን በሚሉት የአንድነት/መድረክ አመራር አባላት ላይ ሰፊ ዘመቻ እያካሄዱ ሲሆን፣ የአሰብን ጉዳይ አታንሱብኝ እያለ የአልጀርሱን ስምምነት ፈርሞ ያፀደቀውንና የሔጉንም ፍ/ቤት ውሳኔ ለተቀበለው ለጠ/ሚ መለስ ቡድን የፕሮፓጋንዳ ድጋፍ በመስጠት ላይ ናቸው። ታዲያ አቶ ተስፋዬ ማን ናቸው? የኢትዮጵያ ወይስ የኤርትራ ጥቅም አስከባሪ ፕሮፓጋንዲስት? ...” ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደራሲው ማስታወሻ - የመጽሐፍ አቃቂር

Yederasiw Mastawesha የደራሲው ማስታወሻተስፋዬ ዮሐንስ

... ተስፋዬ ‘የባርነት’ ዘመኑን በመቃኘት ያሳለፈውን ህይወት፣ ገጠመኙን፣ የታዘባቸውን፣ ወዘተ፣ በጭልፋ እየቆነጠረ ያቋድስ ጀመር። ‘የጋዜጠኛው ማስታወሻ’ የተባለውን መጽሐፍ ደርሶ ለንባብ አበቃ። ብዙዎች አበጀህ፣ ደግ አደረግ አሉት። ቀጣፊ ያሉትም ነበሩ። ኤርትራዊ የዘር ሃረጉን በመቁጠር የሻዕቢያ ደጋፊ ያሉትም አልጠፉም። በተለይ የኢህአዴግ ደጋፊዎችና አባላት፣ ገበና አጋለጠ በማለት ብዙ ጽፈውበታል። ሙሉ በሙሉ ከባርነት በወጣበት ‘የጋዜጠኛው ማስታወሻ’ መጽሐፉ ላይ የብዙ ሰዎች ስሞች ተነስቶ ተስፋዬ ከበድ ከበድ ያሉ ክሶችና ውንጀላዎች ደረድሮአል። አንዳቸውም አላስተባበሉም። ለምን? ... ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ ተስፋዬ ሌላ መጽሐፍ ደርሶ ለንባብ አብቅቷል፤ ‘የደራሲው ማስታወሻ’። መጽሐፉ 25 ራሳቸውን የቻሉ ክፍሎች አሉት። ይህ አቃቂር በሦስት ዐብይት ጉዳዮች ላይ ያተኩራል። 1/ መጽሐፉን መድረስ ለምን አስፈለገ? 2/ መጽሐፉ ያቀፋቸው ዋና ዋና ጭብጦች ምንድናቸው? 3/ የመጽሐፉ ደካማ ጎኖችስ? ... ሙሉውን አስነብበኝ ...