ረቡዕ ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ኀዘናቸውን ለመግለጽ አደባባይ የወጡ ኢትዮጵያውያን በፌዴራል ፖሊስ ሲደበደቡ የሚያሳይ አስተያየትና ዜና ዘገባ ያሌለበት ቪዲዮ።
ሮይተርስ ረቡዕ ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ኀዘናቸውን ለመግለጽ አደባባይ የወጡ ኢትዮጵያውያን በፌዴራል ፖሊስ መደብደባቸውን እንዲህ ዘግቦታል።
ረቡዕ ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ኀዘናቸውን ለመግለጽ አደባባይ የወጡ ኢትዮጵያውያን በፌዴራል ፖሊስ መደብደባቸውን በኢንተርኔት የተለቀቁ የቪዲዮ ምስሎች አመለከቱ፣ አልጀዚራ እንዲህ ዘግቦታል።
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ የአማርኛው ክፍል በሊቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ክርስቲያን ወገኖቻቸውን እየታደጉ መሆኑ ዘገበ።
ፈረንሣይ 24 የተሰኘው የፈረንሣይ ቴሌቭዥን ጣቢያ በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ የኃይማኖት ተቋማት መሪዎች በጋራ በመሆን አይሲስ በሊቢያ በስደት በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ያደረሰውን ጭፍጨፋ ማውገዛቸውን ዘገበ። የኢትዮጵያ መንግሥት የተገደሉት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ማረጋገጡን አክሎ ዘግቧል። የሟቾችን ቤተሰቦችንም ቃለምልልስ አድርጎላቸዋል።
ናይጄሪያዊቷ ጋዜጠኛ አዴኦላ ፋዩን በአፍሪካ ወቅታዊ ዜናዎች ላይ ተመስርታ በአሸሟሪነት ትታወቃለች። ነዋሪነትዋ በዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ሲሆን፣ በሣምንት አንዴ በሳህራ ቲቪ ”Keep It Real With Adeola” በተሰኘው ዝግጅቷ ነው የምታሸሙረው። ከዚህ ቀደም የቀድሞዋን ቀዳማዊ እመቤት አዜብ መስፍንን አስመልክታ ባቀረበቻቸው ዝግጅቶች በብዙ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ትታወቃላች። በዚህ ቪዲዮ የአፍሪካ መንግሥታትን ሙሰኝነት አስመልክታ ታሽሟጥጣለች።
ሙሉውን አስነብበኝ ..."ፍራንስ 24" የተሰኘው የቴሌቭዥን ጣቢያ ዛሬ ዓርብ መጋቢት 4 ቀን 2007፣ ማርች 13 ቀን 2015 ሪፖርተርስ በተኘው ዝግጅቱ ስለየሕዳሴው ግድብ የ16 ደቂቃ ጥናታዊ ሪፖርት አቅርቧል። ለመመልከት የማጫወቻ ቁልፉን ይጫኑ!