የታሪክ ዘይቤ (ብዕለ ስብሐትሁ ወጥበቢሁ!)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ሰሎሞን ተሠማ ጂ.

በመጀመሪያ፣ አንድ ሰው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በመጓዝ ላይ ሳለ፣ በአጋጣሚ አንድ ወርቃማ-ቁልፍ ቢጥል በዚያው መንገድ እንደሚመለስ አያጠራጥርም። ሰውዬው የጠፋበትን ቁልፍ ለማንሳት የፈለገውን ያህል ጊዜ (ዘመን) ቢቆይም እንኳ፣ ቁልፉን ፍለጋ በዚያው በተጓዘበት መንገድ ይመለሳል። እንጂ በሌላ አቋራጭ-መንገድ አይሄድም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፋሲካ - “ሥጋዊ ወመንፈሳዊ”

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ኤፍሬም እሸቴ - ኢትዮጵያዊ

በኢትዮጵያውያን ዘንድ በታላቅ ሁኔታ ከሚከበሩት በዓላት መካከል ትንሣኤ ወይም ፋሲካ አንዱና ዋነኛው ነው። ሃይማኖታዊ ትርጓሜው እና ምንነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ባህላዊ አከባበሩ እና ምንነቱም ከኢትዮጵያውያን ባህላዊ ማንነት ጋር በጥልቅ የተያያዘ ነው። እንኳን በአገር ቤት ያለው በሰው አገር ያለነውም እንኳን ብንሆን እንደ አቅሚቲ የአገር ቤቱን መንፈስ በያዘ ሁኔታ እናከብራለን። ስለዚህ ፋሲካው መንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን ሥጋዊ/ ባህላዊ አንድምታው ከፍ ያለ ነው ማለት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሐተታ አድዋ - በዕውቀቱ ስዩም (ደራሲና ገጣሚ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

የአድዋ ድልን ከድንበር ሉአላዊነት ጋር አያይዞ መተንተን የተለመደ ነው። ድሉ አነሠ በዛ የሚለው ጭቅጭቅ ከዚህ መሠረት ይፈልቃል። በኔ ግምት የአድዋ ድል ትልቅ ጭብጥ ‹‹የሰውነት ክብር›› ይሰኛል። ቀደምቶቻችን ወደ አድዋ የጋለቡት በግፍ የተነጠቁትን የሰውነት መታወቂያ ለማስመለስ ነው። እንዲያውም ሰው መሆናቸውን በማያዳግም መንገድ ያረጋገጡት አድዋ ላይ ነው ማለት ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደመራ ታሪክ (ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ደመራ በኃይማኖታችን፣ በታሪካችን እና በባሕላችን አንጻር

ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. መስከረም ፳፻፬ ዓ.ም.

‘ደመራ’ ደመረ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተወሰደ ነው። ትርጉሙ ጭመራ ማለት እንደሆነ ለማንም ግልጽ ነው። ጥሪት (ካፒታል) እንዳይጎድል እንዳይቀነስ ይልቁንም እየበዛና እያደገ እንዲቀጥል ጠብቆ መያዝ የሚያስችል ደመራ ነው። ስሙ እንደሚያመለክተው ማስታወሻነቱ ለተጠራቀመ፣ ለተሰበሰበና ለተጨመረ ነገር ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጣልያን ውድቀት (ጌቱ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

የጎንደር ጦርነት የአርበኞች ድል የፋሽስት ጣልያን የመጨረሻ ውድቀት

ኃብተሥላሴ ስለሺ (ጌቱ) ከፓሪስ - ፈረንሣይ

ወራሪው የፋሽስት ጣልያን ጦር በጀግኖች አርበኞች ተጋድሎና በእንግሊዝ ረዳትነት ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ድል ሆኖ አዲስ አበባን ከለቀቀ በኋላ፤ የተቀረው የጠላት ጦር የምስራቅ አፍሪካ የጣልያን ጦር የበላይ አዛዥ በሆነው በዱክ ዲዎስታ አመራር ስር ደሴ ላይ መሽጎ ሲጠባበቅ፤ የቀረው ጦር እንዲሁ የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ጦር አዛዥ በሆነው በጄኔራል ናዚ አመራር ጎንደር ላይ መሽጎ የሙሶሎኒን እርዳታ ይጠባበቅ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዓድዋ ድልና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

የዓድዋ ድልና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪካዊ ድርሻና ውለታ

ፍቅር ለይኩን ከደቡብ አፍሪካ

የዓድዋ ድልን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ን በስንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ በማኅበረ ቅዱሳን የምርምርና የጥናት ማእከል ድሉን አስመልክቶ ቤተ ክርስቲያኒቱ የነበራትን ሚና ለማዘከር በአዲስ አበባ በብሔራዊ ሙዚየም የተደረገውን ውይይት ዜና በደጀ ሰላም ማንበቤ በውስጤ አንድ ስሜት አጫረብኝ፤ እናም ስለ ድሉና ቤተ ክርስቲያናችን ስለነበራት ታላቅ ድርሻና ወለታ ጭምር ጥቂት ለመጨመር አስብኩና ብዕሬን አነሳሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዝክረ አድዋ በኪነጥበብ መወድስ (ዳንኤል አበራ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ዳንኤል አበራ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

ኢትዮጵያ ከዘመነ መሣፍንት ተላቅቃ አንፃራዊም ቢሆን ወደ ተረጋጋ ማዕከላዊ አስተዳደር የተሸጋገረችበት ዘመን። አባ ዳኘውም እምዬም እየተባሉ ሲጠሩ የነበሩት አፄ ምኒልክ ሥልጣን ያደራጁበት እና ኢትዮጵያን ያሰሱ አውሮፓውያንን ባላሰለሰ የመሣሪያ ስጦታም ግዢም ጥያቄ የወተወቱበት ዘመን፤ ኋላም ተክለፃዲቅ መኩሪያ እንደጻፉልን “ባመጣው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ ተፈጠመ ጣሊያን አበሻ እንዳይደርስ” ከተባለበት የጣሊያን መንግሥት ጭምር የመሣሪያ ስጦታ ተረክበው ምኒልክ ጦራቸውን ያደራጁበት ዘመን፤ አውሮፓውያን አህጉራትን እንደቅርጫ ሥጋ የተከፋፈሉበት ዘመን። አፍሪካም፣ ኢትዮጵያም የዚህ ዕጣ ፈንታ ተቋዳሽ እንዲሆኑ በዝግ ተወስኖ ለአፄ ምኒልክና መንግሥታቸው መልዕክት የተነገረበት ዘመን፤ አፄ ምኒልክም መልዕክቱን ሰምተው እግዜር ይስጥልኝ ውሳኔያችሁን አልቀበልም ያሉበት፣ የጦርነትም ስጋት ያንዣበበት ዘመን ነበር ዘመኑ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዓለ መስቀል

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረስዎ! … “መስከረም ባበባው ሠርግ በጭብጨባው ይታወቃል” ይላሉ አበው። አንድም መስከረም ርዕሰ ዓውደ ዓመት፣ የዘመን መለወጫ በመሆኑ ወርኃ አደይ ወወርኃ ጽጌ ተብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዛሬ 92 ዓመት ይኼን ጊዜ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

“... በታሪክ መድረክ ሚናቸውን ተጫውተው ያለፉ ሰዎች እንደ ተውኔት ገፀ ባህርያት ናቸው። ስለሆነም የዕለት ተዕለት ሰብዓዊ ግኑኝነቶችም ሆኑ በመሪና ዜጋ መካከል ያለው ግንኙነት ኅሊናችንን ሳይጫነው ልንፈርድባቸውም ሆነ ልንፈርድላቸው ይገባል ...” ያሉት እውቁ የታሪክ ሊቅ ፕሮፌሠር ባህሩ ዘውዴ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...