ከኢካድ ፎረም ተክለሚካኤል አበበ የኢትዮ-ሚዲያ ድረ ገጽ ዋና አዘጋጅ ከሆነው ጋዜጠኛ አብርሃ በላይ ጋር ቃለምልልስ አድርጓል። ቃለምልልሱ በተለይም በአቶ ስዬ አብርሃ፣ በህወሓት እና በትግራይ ህዝብ ጉዳይ ዙሪያ ያተኮረ ነው። ጋዜጠኛ አብርሃ በአሁን ሰዓት የትግራይ ህዝብ ህወሓትን እንደማይወደው በቃለምልልሱ ላይ የገለጸ ሲሆን፣ ከፓርቲው ጋር እየሠሩ ያሉትን ሆነ ሲሰሩ የቆዩት ሰዎች “ፀረ-ኢትዮጵያዊ” መሆናቸውንና ፓርቲውም ፀረ-ኢትዮጵያዊ ድርጅት ነው ሲል ገልጿል። ጠ/ሚ መለስ፤ "ኢትዮጵያዊ አይደለም" ይላል ጋዜጠኛ አብርሃ በቃለምልልሱ።

 

በቃለምልልሱ ላይ “… ደርግ ከገደለው የትግራይ ህዝብ፤ ወያኔ/ህወሓት የገደለው የትግራይ ህዝብ ቁጥር ይበልጣል” የሚሉ የህወሓት የሽምቅ ተዋጊዎች እንዳሉ ገልጿል። ሙሉ ቃለምልልሱን ለማየትና ለማድመጥ የማጫወቻውን ይጫኑ!

 

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ