ዘመቻ #MeToo ወይንም #እኔንምገጥሞኛል
የ#እኔንምገጥሞኛል ዘመቻንና እንዲሁም ኢትዮጵያውያን ሴቶች የሚገጥማቸውንና የሚያልፉበትን ጾታዊ ትንኮሳ፣ ጥቃትና ወከባ ላይ ሐሳባቸውን በፎረም ፷፭ ”ሙጠኖ” (Muxannoo) በተሰኘው ዝግጅት ላይ ያጋሩት ሶልያና ሽመልስ ከዩናይትድ ስቴትስ እና ወ/ሮ አስቴር አስገዶም ከስዊድን ናቸው።
”ሙጠኖ” (Muxannoo) የተሰኘው የፎረም ፷፭ ዝግጅት የሕይወት ተሞክሮን የሚዳስስ ሲሆን፣ #MeToo ወይንም #እኔንምገጥሞኛል የተሰኘውን ዓለምአቀፋዊ የሴቶች የማኅብራዊ ሚድያ ዘመቻ ላይ በዚህ ዝግጅቱ ያተኮረው።
ሙሉውን ውይይት ለማድመጥ፣ የማጫወቻ ቁልፉን ይጫኑ!