የሶማሌ ክልል የመራጮች ምዝገባን በተመለከተ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

National Election Board of Ethiopia (NEBE)

ኦብነግ፣ ነፃነት እና እኩልነት፣ ኢዜማ እና የግል እጩ ተወዳዳሪዎች ለቦርዱ አቤቱታዎች አቅርበዋል

ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ 2013 የመራጮች ምዝገባ ሒደት ላይ ከፍተኛ አቤቱታ የቀረበበት በሶማሌ ክልል እየተከናወነ ያለው የመራጮች ምዝገባ ሒደት ነው። በዚህ ሒደት ላይ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ለቦርዱ አቤቲታዎችን ያቀረቡ ሲሆን፤ (ኦብነግ፣ ነፃነት እና እኩልነት፣ ኢዜማ እና የግል እጩ ተወዳዳሪ)፣ ሕጋዊ ያልኾነ የምዝገባ ሒደትን የሚያሳዩ ምስሎች እና ቪዲዎችም በማኅበራዊ ሚዲያዎች ሲታዩ ነበር፤ ቦርዱም በሚዲያ ሞኒተሪንግ ክፍሉ ተሰበስቦ ቀርቦለት እነዚህን ምስሎች እና ቪዲዮዎች ተመልክቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመራጮች ምዝገባን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

National Election Board of Ethiopia (NEBE)

የመራጮች ምዝገባ ከመጋቢት 16 እስከ ሚያዝያ 15 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ይከናወናል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳን አውጥቶ ተግባራትን እያከናወነ እንደኾነ ይታወቃል። ከዚህም መካከል በአሁኑ ወቅት እየተከናወነ ያለው የእጩዎች ምዝገባ አንዱ ሲሆን፤ በጊዜ ሰሌዳው መሠረት ተከታዩ ዋና ተግባር የመራጮች ምዝገባን ማከናወን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኦሮሚያ፡ ሙሐመድ ዴክሲሶ በአፋጣኝ ከእስር ሊለቀቅ ይገባል

The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC)

በኦሮሚያ ክልል የፍርድ ቤቶች ትእዛዝ አለመከበሩ አሁንም አሳሳቢ ነው

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከየካቲት 6 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በጅማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ወረዳ 1 ፖሊስ ጣቢያ በእስር ላይ የሚገኘውን ሙሐመድ ዴክሲሶ በተመለከተ የጅማ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት የካቲት 16 ቀን 2013 ዓ.ም. በዋስ እንዲለቀቅ ያሳለፈውን ውሳኔ በመተላለፍ፤ ከእስር አለመለቀቁ እንዳሳሰበው ገልጾ፤ ሙሐመድ ዴክሲሶን ጨምሮ ሌሎችም በፍርድ ቤት የዋስትና መብት ተከብሮላቸው በእስር ላይ የሚገኙ እስረኞች በአፋጣኝ እንዲለቀቁ አሳስቧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“መልካም እድል ለተወዳዳሪዎች” ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ

Birtukan Mideksa

የተከበራችሁ የፓርቲዎች አመራር አባላት፣ የፓርቲ እጩ ተወዳዳሪዎች እና በግላችሁ የምትሳተፉ እጩዎች!!!

ዛሬ ለ6ኛው አጠቃላይ ምርጫ በእጩነት ስትመዘገቡ ወይም እንደ ፓርቲ እጩዎቻችሁን ስታስመዘግቡ ከፊታችን ያለው መንገድ ከፊል ተስፋ ከፊል ሥጋትን አዝሎ እንደሚጠብቃችሁ እንደሚጠብቀን ለሁሉም ግልጽ ነገር ይመስለኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በማይካድራ የተፈጸመው ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ፈጣን ምርመራ የመጀመሪያ ደረጃ (ቀዳሚ) ሪፖርት (ኢሰመኮ)

The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC)

(Preliminary Findings Report) የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን - ኅዳር 15 ቀን 2013 ዓ.ም.

መግቢያ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን ውስጥ በምትገኘው ማይካድራ ከተማ ውስጥ ተፈጸመ የተባለውን የብዙ ሰዎች ግድያ ወንጀልና የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ለማጣራት የሰብአዊ መብቶች ባለሞያዎች የምርመራ ቡድን ወደ ቦታው በመላክ ፈጣን ምርመራ አካሂዷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"የሐጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ ግድያና ጥቃት የተፈጸመው በኦርቶዶክሳውያን ላይ ነው" የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ

የልጃችን የሐጫሉ ሁንዴሳን ግድያ እና ግድያውን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በአንዳንድ ዞኖች ተቀነባብረው በተፈጸሙ ጥቃቶች የተጎዱ ኦርቶዶክሳውያንን መርዳትንና መልሶ ማቋቋምን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

“አማን አማን እብለክሙ ከመ ትበክዩ ወትላህዉ አንትሙ፤ ወዓለምሰ ይትፌሣሕ፤ ወአንትሙሰ ተኃዝኑ፤ ወኃዘንክሙ ፍሥሐ ይከውነክሙ" እውነት እውነት እላችኋለኹ፤ እናንተ ታለቅሳላችኹ፤ ሙሾም ታወጣላችኹ፤ ዓለም ግን ደስ ይለዋል፤ እናንተም ታዝናላችኹ፤ ነገር ግን ኃዘናችኹ ወደ ደስታ ይለወጣል።” (ዮሐ.16፥20)

ሐጫሉ ሁንዴሳ ስመ ጥምቀቱ ኃይለ ገብርኤል፣ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ምሽት በአዲስ አበባ መገደሉ ይታወሳል። ቤተ ክርስቲያን፥ በዚያድንገተኛ የልጇ ግድያ ከባድ ኃዘን ተሰምቷታል። ኾኖም፣ በግድያው የተሰማትን ኃዘን ለመወጣት ጊዜ ሳይሰጣት፣ ኃዘንተኛነቷ ተረስቶ እናእንደ ጠላት ተቆጥራ፣ በኦሮሚያ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች በክርስቲያን ልጆቿ ላይ ዘግናኝ ፍጅት እና መከራ ተፈጸመባቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት የአገሪቱን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ብቻውን የመፍታት አቅም የለውም!

የአብሮነት መግለጫ

ከአብሮነት ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት (#አብሮነት) የተሰጠ መግለጫ

አብሮነት ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት (አብሮነት) ባለፉት ጊዜያት የአገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታዎች እየተከታተለ እና እየገመገመ አቅጣጫ የሚያሳዩ መግለጫዎችን ሲያወጣ መቆየቱ ይታወሳል። አብሮነት በነዛ ሁሉ ጊዜያት የለውጥ ሒደቱ ሃዲዱን እየሳተ መሆኑን እና አገራችን የሕልውና አደጋ ውስጥ ከመውደቋ በፊት ተጨባጭ የመፍትሔ እርምጃዎች እንዲወሰዱ አማራጭ መፍትሔ ጭምር በማስቀመጥ ሲወተውት ቆይቷል። ነገር ግን የለውጥ ኃይል ነኝ ባዩ መንግሥት ከኔ ውጭ መፍትሔ ላሳር፤ የማሻግራችሁም እኔ ብቻ ነኝ በሚል መታበይ የቁልቁለት ጉዞን መርጧል። በዚህ የመንግሥት ፍጽም የሆነ አንባገነናዊ ባሕርይም የተነሳ አገራችን አሁን የምትገኝበት ሁኔታ ለውጡ ከመምጣቱ በፊት ከነበረው ሁኔታ ጋር እጅግ ተመሳሳይ ነው። ከዚህም የከፋ የሕልውና አደጋ ተጋርጦብናል። በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግሥት ሕግና ስርዓትን ማስፈን እየተሳነው በየአካባቢው ንጹኀን ኢትዮጵያዊያን ማንነትን እና ኃይማኖትን ማዕከል ባደረገ ጥቃት ሕይወታቸውን እያጡ ነው፣ አካላቸው እየጎደለ ነው፣ ጥሪታቸውን አሟጠው ያፈሩት ሀብትና ንብረት እየወደመ ነው። በአገር ውስጥና በአለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ዘር ጭፍጨፋ/ጄኖሳይድ ነው ብለው በገለፁት በዚህ አሰቃቂ ድርጊት ዜጎች ተንቀሳቅሶ ሀብትና ንብረት የማፍራት ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸው አደጋ ላይ ወድቋል። የዜጎች ለዘመናት የተገነባው የመቻቻል፣ የመከባበር፣ የመተዛዘን አኩሪ ባህላችን እየተደፈቀ ዘረኝነት፣ ጎጠኝነትና መንደርተኝነት ከምንግዜውም በላይ ነግሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ