መንግሥት በእርዳታ ስም በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የሚገቡ አካላትን እንደማይታገስ አስታወቀ

Ambassador Redwan Hussein

በሰብአዊ እርዳታ ስም ለሕወሓት ቡድን መሣሪያ ለማስታጠቅ የሚደረጉ ሙከራዎች መኖራቸው ተገለጸ

ኢዛ (ሐሙስ ሐምሌ ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 15, 2021)፦ በእርዳታ ስም ወደ ኢትዮጵያ ገብተው፤ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የሚገቡ አካላትን መንግሥት የማይታገስ እና የአሸባሪው የሕወሓት ቡድን ሕፃናትን ለውትድርና እየማገደ መኾኑን እያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ነገሩን በአወንታ መመልከታቸው ፍጹም ተቀባይነት እንደማይኖረው የኢትዮጵያ መንግሥት ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ ሕዝቡ ከመከላከያ ሠራዊቱ ጋር እንዲኾን ጠየቁ

L. Gen. Bacha Debele

ሠራዊቱ ማጥቃት እንዳለበት ወስኖ እየሠራበትም ነው ብለዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሐምሌ ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 14, 2021)፦ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ ከዚህ ቀደሙ ከመከላከያ ሠራዊቱ ጐን እንዲቆም የአገር መከላከያ ሠራዊት የሠራዊት ግንባታ ሥራዎች ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ ገለጹ። ጁንታው ትንኮሳውን መቀጠሉንም ሌ/ጄኔራሉ በወቅታዊ ሁኔታ ላይ ማምሻውን በሰጡት ተጨማሪ መረጃ፤ ሕዝቡ መገንዘብ አለበት ብለው የገለጹት ደግሞ ወታደራዊ ሥራ በወታደር እንጂ በአክቲቪስቶች የሚከናወን አለመኾኑን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጸጥታ ኃይሉ ወደ ማጥቃት እንዲሸጋገር የአማራ ክልል ትእዛዝ ሰጠ

ግዛቸው ሙሉነህ

“የተከፈተብን መጠነ ሰፊ ወረራ የሕልውና ጉዳይ በመኾኑ የክልሉ መንግሥት የትኛውንም ዐይነት አፍራሽ ግብ ያላቸውን አካላት እኩይ ሴራ አይታገስም” የአማራ ክልል መንግሥት

ኢዛ (ረቡዕ ሐምሌ ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 14, 2021)፦ የሕወሓት የሽብር ቡድን በተከፈተበት ይፋዊ ጦርነት ራሱን ከመከላከል ወጥቶ ወደ ማጥቃት ለመሸጋገር መወሰኑን የአማራ ክልላዊ መንግሥት አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጁንታው የኢትዮጵያ ሕልውና ቀንደኛ ጠላት መኾኑን ገለጹ

PM Abiy Ahmed

“ጁንታው ሕፃናትና ወጣቶችን በአደንዛዥ ዕጽ እያሳበደ ወደ ጦርነት እየማገደ ይገኛል” ዶ/ር ዐቢይ

ኢዛ (ረቡዕ ሐምሌ ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 14, 2021)፦ “ጁንታው የኢትዮጵያ ሕልውና ቀንደኛ ጠላት መኾኑን ደግሞ እያስመሰከረ ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሰጡት መግለጫ አስታወቁ። ጁንታው ሕፃናትና ወጣቶችን በአደንዛዥ ዕጽ እያሳበደ ወደ ጦርነት እየማገደ ይገኛል ሲሉም ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሽብር የተፈረጀው ሕወሓት መሠረተ ሰፊ ወረራና ጥቃት ማድረግ መጀመሩን የአማራ ክልል አስታወቀ

TPLF

ወረራውን ለመቀልበስ ጥሪ ተላልፏል

ኢዛ (ማክሰኞ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 13, 2021)፦ በሽብርተኝነት የተፈረጀው የሕወሓት ቡድን የኢትዮጵያ መንግሥት በአንድ ወገን የወሰደውን የተኩስ አቁም ውሳኔ እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም፤ በኢትዮጵያና በአማራ ሕዝብ ላይ መሠረተ ሰፊ የኾነ ወረራና ወታደራዊ ጥቃት ማድረግ መጀመሩን የአማራ ክልላዊ መንግሥት አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብልጽግና አሸናፊ መኾኑ ተረጋገጠ

Ethiopian Election 2021 result

ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 410 ወንበሮችን አሸንፏል
ኢዜማ አራት፣ አብን አምስት፣ ጌሕዴፓ ሁለት ወንበሮች አግኝተዋል

ኢዛ (ቅዳሜ ሐምሌ ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 10, 2021)፦ በስድስተኛው አገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ የኾነ የምርጫ ውጤቱን ያስታወቀ ሲሆን፤ በሁሉም የምርጫ ክልሎች ብልጽግና ፕርቲ አሸናፊ መኾኑን አረጋግጧል። ብልጽግና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 410 ወንበሮች አግኝቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያን ባለ ድል ያደረገው የጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔ

Seleshi Bekele (PhD. Eng.), the Minister of Water, Irrigation and Energy of Ethiopia

በደቂቃዎች ገለጻ እውነቱን በማሳወቅ የግብጽ ሴራን አክሽፏል
ከዚህ በኋላ ድርድሩ በአፍሪካ ሕብረት በኩል ብቻ ይካሔዳል

ኢዛ (ዓርብ ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 9, 2021)፦ ከኢትየጵያ ወቅታዊ አጀንዳዎች መካከል አንዱ የኾነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ በግብጽና በተባባሪዎቿ የጸጥታው ምክር ቤት ዘንድ ቢቀርብም፤ ከሳሾችዋ እንዳሰቡት ሳይኾን ኢትዮጵያ ድል ያደረገችበት ኾኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዋጋ ግሽበቱ ወደ 25 በመቶ እያሻቀበ ነው

Central Statistics Agency, Ethiopia

የሰኔ ወር የዋጋ ግሽበት መጠን እስከ ዛሬ ያልተመዘገበ ነው
የምግብ ነክ ምርቶች የዋጋ ግሽበት ከ28 በመቶ በላይ ወጥቷል

ኢዛ (ሐሙስ ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 8, 2021)፦ በማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ መሠረት የሰኔ ወር የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ24.5 (ሃያ አራት ነጥብ አምስት) በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንና የምግብ ዋጋ ግሽበት ደግሞ በ28.7 (ሃያ ስምንት ነጥብ ሰባት) በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢድና ሞል በ810 ሚሊዮን በጨረታ ተሸጠ

EDNA Mall

በባንክ እዳ የቀረበውን ሕንጻ ጨረታ ያሸነፈው የቻይና ኩባንያ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 7, 2021)፦ “ኢድና ሞል” በመባል የሚታወቀው እና በተክለብርሃን አምባዬ ባለቤትነት የተያዘው ሕንጻ ባለበት የባንክ እዳ፤ ለጨረታ ቀርቦ አንድ የቻይና ኩባንያ 810 ሚሊዮን ብር ዋጋ ሰጥቶ አሸናፊ ስለመኾኑ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዋሽ ባንክ በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት 5.58 ቢሊዮን ብር አተረፈ

Awash Bank

ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ሒሳብ መጠን በማስመዝገብ በግል ባንኮች ታሪክ አስመዘገበ

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. July 6, 2021)፦ በተጠናቀቀው የ2013 ዓ.ም. በጀት ዓመት አምስት ነጥብ አምስት ስምንት (5.58) ቢሊዮን ብር ማትረፉን አዋሽ ባንክ በዛሬው ዕለት አስታወቀ። ከግል ባንኮች የተጠናቀቀውን የሒሳብ ዓመት ሪፖርት በማቅረብ ሁለተኛው የግል ባንክ ኾኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ