የአማራ ብልጽግና ወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምትና ራያን በተመለከተ ማስጠንቀቂያ ሰጠ

Amhara Prosperity Party

ፓርቲው እስከዛሬ ካወጣቸው መግለጫዎች ውስጥ እጅግ ጠንካራ ነው

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 29, 2021)፦ የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምትና ራያ በራሳቸው መሥዋእትነት ነፃነታቸውን ያስከበሩ የአማራ አካባቢዎች መኾናቸውን እናሳውቃለን ሲል የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ። ፓርቲው እስከዛሬ ካወጣቸው መግለጫዎች ውስጥ እጅግ ጠንካራ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት በትግራይ ክልል የተናጠል የተኩስ አቁም አወጀ

Office of the Prime Minister

የእርሻ ወቅት እስኪጠናቀቅ ድረስ ይቆያል የተባለው ተኩስ አቁም ከዛሬ ከሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ይጀምራል

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፳፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 28, 2021)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በትግራይ ክልል ካለምንም ቅድመ ሁኔታ የተናጠል የተኩስ አቁም ማወጁን አስታወቀ። የተኩስ አቁሙ የእርሻ ወቅት እስኪጠናቀቅ ድረስ ይቆያል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድ የግል ተወዳዳሪ የድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ ባለመካተቱ ከ100 በላይ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫ ታገደ

Birtukan Mideksa

በኦሮሚያ ክልል በነገሌ በእነዚህ ምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በድጋሚ ይካሔዳል

ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 24, 2021)፦ በኦሮሚያ ክልል በነገሌ ምርጫ ክልል ከ100 በላይ በሚኾኑ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው እንዳይካሔድ የተላለፈን መመሪያ በመጣስ በመካሔዱ በእነዚህ ጣቢያዎች የተደረገው ምርጫ 2013 ተቀባይነት እንደማይኖረው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ገለጸ። ይህ የተፈጠረበት ምክንያት ምርጫ ቦርድ ድምፅ መስጫ ወረቀቱ ላይ በግል የተወዳደሩትን ግለሰብ ባለማሳተሙ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢዜማ አጋጠሙ ያላቸውን ችግሮች ገለጸ

Birhanu Nega (Prof.)

ዘግይተው ምርጫ የተጀመረባቸው ቦታዎች ሰዓት እንዲጨመር ጠይቋል

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 21, 2021)፦ በዛሬው ምርጫ 2013 ላይ ጥሩ ነገሮች እንደታዩ ሁሉ፤ የተለያዩ ችግሮችንም መመልከቱን ኢዜማ አስታወቀ። ዘግይተው ምርጫ የተጀመረባቸው ቦታዎች ሰዓት እንዲጨመር ጠይቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የጠዋት ቅኝትና የቀትር በኋላ ድምፅ መስጠት

PM Abiy Ahmed

2070 የሚዲያ ባለሙያዎች በ100 ምርጫ ጣቢያዎች ምርጫውን በቀጥታ እያስተላለፉ ነው

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 21, 2021)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ጠዋት በአዲስ አበባ የአንድ ዳቦ ፋብሪካን ግንባታ ጨምሮ፤ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን የሥራ ሒደት ከጎበኙ በኋላ፤ ወደ ትውልድ ቀያቸው በመሔድ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢዜማ በምርጫው ቀን ላይ ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሊሰጥ ነው

Ethiopian Citizens for Social Justice

በቀሩት ሰዓታት መፍትሔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች አሉ ብሏል

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 21, 2021)፦ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በ2013 ምርጫ ቀን ላይ ያጋጠሙ እና በተቀሩት ሰዓታት መፍትሔ ይገባቸዋል ባላቸው ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት ጥሪ አቀረበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወይዘሪት ብርቱካን በአማራና በደቡብ ክልሎች ሕገወጥ ተግባሮች ታይተዋል አሉ

Birtukan Mideksa

- በደቡብ የምርጫ መገልገያ የያዘ ሳጥን በመሰረቁ፣ የምርጫ ጣቢያው አልተከፈተም
- ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም ጠይቀዋል

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 21, 2021)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫ 2013 አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች ሕገወጥ ተግባራት መታየታቸውን አመለከቱ። በደቡብ ክልል “ኡባ ደብረፀሐይ” በተሰኘ የምርጫ ጣቢያ፤ ለጣቢያው የሚያገለግል ሰማያዊ ሳጥን ተሰርቋል መሰረቁን ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫው እየተካሔደ ነው

ምርጫ 2013

ረዣዥም ሰልፎች በየቦታው እየታዩ ነው
የምርጫ ሒደቱ አለመፍጠን ቅሬታ እያስነሳ ነው

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 21, 2021)፦ ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ 2013 ዛሬ ማለዳ ምርጫ በሚካሔድባቸው የአገሪቱ ክፍሎች ድምፅ መሰጠት ቢጀምርም በብዙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ሒደቱ ፈጣን ካለመኾኑ ተያይዞ መራጮች ቅሬታ እያቀረቡ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ