ገፍታሪዋ የወርቅ ሜዳሊያውን ተነጠቀች

Gelete Burka (C) of Ethiopia is helped by medical staff after crossing the finish line last following a fall in the women's 1500 meters final during the world athletics championships at the Olympic stadium in Berlin, August 23, 2009.

Ethiopia Zare (እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. August 23, 2009)፦ በሴቶች 1500 ሜትር ርቀት ውድድሩን እስከ 1200 ሜትር ስትመራ የነበረችው አትሌት ገለቴ ቡርቃ በስፔይኗ አትሌት ናታሊያ ሮድሪከዝ ተገፍትራ መሬት ላይ በመውደቅዋ ውድድሩን ሳታሸንፍ ቀርታለች። ናታሊያ ውድድሩን በአንደኝነት ብትጨርስም ዳኖቹ አሸናፊነትዋን ውድቅ በማድረግ የወርቅ ሜዳሊያውን እንዳታገኝ አድርገዋል።

 

BERLIN: Gelete Burka of Ethiopia competes next to other athletes in the women's 1500 Metres Heats during day four of the 12th IAAF World Athletics Championships at the Olympic Stadium on August 18, 2009 in Berlin, Germany.

አትሌት ገለቴ ዛሬ እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. በተደረገው በዚህ ውድድር አሸናፊ ትሆናለች ተብሎ ትልቅ ግምት ተሰጥቷት ነበር። አትሌቷ ስትመራ በነበረችው ውድድር ላይ ተገፍታ ብትውድቅም፤ ከወደቀችበት ተነስታ ውድድሩን በ4 ደቂቃ ከ11፡21 ሰከንድ 11ኛ ሆና ለመጨረስ ተገድዳለች። ስፔናዊቷ አትሌት ውጤቷ ውድቅ በመደረጉ የአትሌት ገለቴ ውጤት 10ኛ ሆኗል። ሌላዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ቃልኪዳን ግዛኸኝ በ4 ደቂቃ ከ08፡81 ሰከንድ አስረኛ ሆና የጨረሰች ቢሆንም በተደረገው የውጤት ማስተካከያ ዘጠነኛ ሆናለች።

Natalia Rodriguez (R) of Spain holds the hand of Gelete Burka of Ethiopia. August 23, 2009.

በቴሌቭዥን በቀጥታ ለመላው ዓለም ሲተላለፍ በነበረው በዚሁ ውድድር ላይ ስፔናዊትዋ አትሌት ናታሊያ አትሌት ገለቴን ገፍትራ የጣለቻት የሚመስል ቢሆንም፤ አትሌት ናታሊ ከውድድሩ በኋላ በሰጠችው ቃለምልልስ ላይ “ቀድማ የገፈተረችኝ ገለቴ ናት” ስትል ተደምጣለች።

Natalia Rodriguez of Spain holds back tears after winning in the women's 1500 metres final during the world athletics championships at the Olympic stadium in Berlin, August 23, 2009. Gelete Burka of Ethiopia was leading the race but stumbled and Rodriguez won. Rodriguez disqualified & lost the Gold.

አትሌት ናታሊያ ውድድሩን የጨረሰችው በ4 ደቂቃ ከ03፡36 ሰከንድ የነበረ ቢሆንም፤ ውጤቷ አይመዘገብላትም። በዳኞቹ ውሳኔ የውጤት ማስተካከያ መሠረት በ4 ደቂቃ ከ03፡74 ሰከንድ ሁለተኛ የገባችው በትውልድ ኢትዮጵያዊት የሆነችውና የባህሬኗ ማሪያም የሱፍ ጀማል የአንደኝነት ቦታውን በመያዝ የወርቅ ሜዳሊያውን አግኝታለች። በዚህ የውጤት ማስተካካያ መሠረት እንግሊዛዊቷ ሊሳ ዶብሪስኪ በ4 ደቂቃ ከ03፡75 ሰከንድ የብር ሜዳሊያ፣ አሜሪካዊቷ ሻኖን ሮበሪ በ4 ደቂቃ ከ04፡18 ሰከንድ የነኀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል።

 

የ24 ዓመትዋ ወጣት አትሌት ማሪያም የሱፍ ጀማል በርካታ ኮከብ አትሌቶችን ባፈራችው አርሲ ውስጥ ክርስቲያን ከሆኑ ኦሮሞ ወላጆችዋ መስከረም 6 ቀን 1976 ዓ.ም. ሲሆን፣ መጠሪያ ስሟ (የቀድሞ) ዘነበች ቶላ ነበር። እ.ኤ.አ. 2004 የበጋ ኦሎምፒክ ውድድር ሟሟያ ሰዓቱን ብታስመዘግብም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኦሎምፒኩ እንዳትሳተፍ ካደረጋት በኃላ ወደ ስዊዘርላንድ ከባለቤትዋ ጋር በመሄድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥገኝነት ጠይቃለች።

 

ከትውልድ ሀገሯ ኢትዮጵያ ተሰድዳ ነዋሪነትዋን በስዊዘርላንድ ካደረገች በኋላ ለአሜሪካ፣ ለካናዳና ለፈረንሣይ ጥንድ ዜግነት አመልክታ በነበረበት ወቅት ነበር በባህሬይን ዓይን ውስጥ የገባቸው። ባህሬን በስፖርቱ ዓለም ምስሏን ለማሳደግ ባቀደችበት ወቅት አትሌቷ ስሟን ወደ ዐረብኛ በመቀየር እ.ኤ.አ. 2006 በኳታር ዶሃ ላይ በተደረገው የእስያ ውድድር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ባህሬንን ወክላ ተወዳድራለች። ምንም እንኳን ስሟን እንድትቀይር ብትደረገም፤ የክርስትና ኃይማኖትዋን ግን እንድትቀይር በባህሬይን አልተገደደችም።

 

ጃፓን ኦሳካ ላይ በተደረገው 11ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናም በ1500 ሜትር አትሌት ማሪያም ለባህሬይን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች። በዚህ በ12ኛውም የሻምፒዮና ውድድር ላይ በርቀቱ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች።

 

ዘጠነኛ ቀኑን የያዘው 12ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል።

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ