”የፍርሃት ከፈን፤ በጎንደር ተቀደደ፤ የጎሕ ብርሃን በኢትዮጵያ ፈነጠቀ!” ጎሕ
Ethiopia Zare (ረቡዕ ሐምሌ 27 ቀን 2008 ዓ.ም. August 3, 2016):- ”የጎንደር ሕብረት” ትናንት ማክሰኞ ሐምሌ 26 ቀን 2008 ዓ.ም. (ኦገስት 2 ቀን 2016 እ.ኤ.አ.)፤ ”የፍርሃት ከፈን፤ በጎንደር ተቀደደ፤ የጎሕ ብርሃን በኢትዮጵያ ፈነጠቀ!” በሚል ርዕስ ያወጣውን ልዩ መግለጫ ለኢትዮጵያ ዛሬ ልኳል። መግለጫው በህወሓት የሚመራው ገዥ ፓርቲን አፈና፣ ጭቆናና በደል የመረረው ህዝብ፤ በተለይ ባላፈው እሁድ ሐምሌ 24 ቀን በጎንደር ከተማ ላይ ህዝባዊው ኃይል የነበረውን የጨለማ ዘመን ገፍፎ መውጣቱን አመላካች መሆኑን ጠቁሟል።