ኢትዮጵያዊነት በዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሣ
ወለላዬ ከስዊድን
ትህትናው እና ሰው አክብሮቱ ምንግዜም የማይለወጠው የከረንት አፌርሱ ያልፋል ቀኑ አንድ ቀን ምሽት ስልክ ደወለልኝ።
“ሀሎ ያልፋል ...”
“ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሣ በከረንት አፌርስ ቃለ መጠይቅ ስለሚደረግለት እንዳያመልጥህ ነው!” ሠላምታም አላስፈለገውም ቸኩሏል።
“አመሰግናለሁ! ያልፋል”
ቃለ መጠይቁ አላመለጠኝም! በሰዓቱ ነበር የደረስኩት። ለብዙ ዓመት የማውቀው የሙያዬ ምስክር ድምፅ ተቀበለኝ። ተያይዞ ዶ/ር ፍቅሬ ለረጅም ሰዓታት የሰጠውን ቃለ መጠይቅ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻው ተከታተልኩ። ታሪኬን እንዳውቅ፣ ኢትዮጵያዊነት መኩሪያ እንደሆነ እንድረዳ፣ ውስጤ የደረቀው እኔነቴ እንዲለመልም አደረገኝ። በኋላ ያልፋል ቀኑ እንዲህ አድርጎ አቀረበው አዳምጡት! ተመልከቱት!