Home ኪነ-ጥበብ ግጥም አጋዚና ሰይጣን (ወለላዬ)
 
አጋዚና ሰይጣን (ወለላዬ) Print E-mail
User Rating: / 6
PoorBest 
Art - ግጥም

አጋዚና ሰይጣን (Read on PDF)

ከወለላዬ ( This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it )

አጋዚና ሰይጣን ተገናኝተው መንገድ

ሽቅብ ቁልቁለቱን በመውጣት በመውረድ

ሲሄዱ አመሹና አንድ ላይ በመጓዝ

ጨለማው ጠንክሮ ዓይናቸውን ሲይዝ

ፈልገው ለማደር በእግዜር እንግዳነት

ፈቃድ ለመጠየቅ ተጠጉ ካንድ ቤት

 

እነዛን እንግዶች ባለቤቱም አይቶ

ከጋብዘ ወዲያ እቤት አስገብቶ

ማሳደር የምችል አንዱን ነው በማለት

ማንነታችውን ጠየቀ እንዲነግሩት

አጋዚው ተነስቶ የመለስ አዲስ ጦር

እንደሆነ ገልጾ አብራርቶ ሲናገር

ሰይጣንም ገለጸ እራሱን ሳይስወር

ይሄኔ ሰውየው ፈገግታ አሳይቶ

እንዲአድር ፈቀደ ሰይጣን እቤት ገብቶ

አጋዚው እራሱን እየነቀነቀ

እንዴት እሱን መረጥክ በማለት ጠየቀ

ሰይጣንስ ይሄዳል በመስቀል በጠበል

አንተ አልወጣም ካልከኝ ምን ማደረግ ይቻላል

ስለዚህ መላህን ያንተን ስለማላውቅ

አላሳድረህም ሌላ ቦታ ጠይቅ

በማለት ተናግሮ ዘግቶ ገባ በሩን

አጋዚን አባሮ አስተኛው ሰይጣንን


 

ከወለላዬ ሰኔ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. ስዊድን

June 23, 2008 Sweden

 

 

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 
የረቡዕ ግጥም ቁጥር ፮

መጀመሪያ ለራስህ ነፃነት ስጥ

ከሱ አገኛለሁ ብለህ አትለማመጥ

መብትህን እራስህ ሳትጠብቅ

አትገረም በእሱ መንጠቅ


በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ