Home መጣጥፍ
መጣጥፍ - Articles
የግንቦት 7 ንቅናቄ ምንድነው? ምንስ አመጣው? ምንስ ሊያመጣ ይፈልጋል? (አንዳርጋቸው ጽጌ) Print E-mail
User Rating: / 10
PoorBest 
Sunday, 29 June 2008 02:59

"የግንቦት 7 ንቅናቄ ምንድነው? ምንስ አመጣው? ምንስ ሊያመጣ ይፈልጋል?" በሚል ርዕስ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሎንዶን ላይ እሁድ ሰኔ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. (ጁን 22 ቀን 2008 እ.ኤ.አ.) ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ባደረገው ህዝባዊ ስብሰባ ላይ ያደረው ንግግር ነው። ሙሉ ንግግሩን በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!

 

 
ግንቦት 7 ንቅናቄ በስዊድን Print E-mail
User Rating: / 13
PoorBest 
Saturday, 28 June 2008 07:13

ህዝባዊ ውይይቱ ምን ይመስል ነበር?

ያሬድ ክንፈ ከስዊድን

ሠላምና ጤናውን ከነቤተሰብህ ያበዛልህ ዘንድ የዘወትር ምኞቴ ነው። ለእመቤትህና ለልጃችሁ የከበረ ሠላምታዬን አቅርብልኝ። ዛሬ የማወጋህ “ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ” የተሰኘውና በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመራው አዲስ ንቅናቄ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከተማ ከህዝብ ጋር ያደረገውን ውይይት ነው። ውይይቱ ቅዳሜ ሰኔ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. እንደሚካሄድ ስላወቅሁ ከስቶክሆልም 220 ኪሎ ሜትር ርቄ ከምኖርበት ሳንድቪከን ከተማ ወደዚያው አመራሁ። ንቅናቄውን በመወከል ዶ/ር ብርሃኑ እና አቶ ቸኮል ጌታሁን ነበር የተገኙት። አቶ ቸኮል የቀድሞው ቅንጅት የላዕላይ ምክር ቤት አባል የነበረ ሲሆን፣ አሁን በስዊድን ስደተኛ ነው።

Read more...
 
ኢህአዴግና የሉዓላዊነት ጉዳይ (ሸዋይልማ ኪዳኔ) Print E-mail
User Rating: / 18
PoorBest 
Monday, 23 June 2008 08:08

ሸዋይልማ ኪዳኔ

ጁን 2008 እ.አ.አ. (ጀርመን)

ጽሑፉን በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ 

 
«እየሮጡ የሚታጠቁት ፖለቲከኞች» (ፕ/ር መስፍን) Print E-mail
User Rating: / 16
PoorBest 
Friday, 20 June 2008 12:57

መስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር) ሰኔ 2000 ዓ.ም.

በቅርቡ በአንድ ጋዜጣ ላይ ስለ ችጋር በተናገርኹት ላይ አንድ ስሙን የማላስታውሰው ሰው፣ ዛሬ ያለውን የገጠሩን ህዝብ የጥጋብ ኹኔታ ባለማወቄ አዝኖልኝ መልስ ሰጥቶ ነበር። ሰሞኑን በውጭ ቴሌቪዥኖች ከትግራይ እስከ ቦረና የተከሠተውን ችጋር በሚያሣቅቅ ኹኔታ ሲያሳዩን ነበር። ይህን በምጽፍበት ጊዜ ትግራይ ውስጥ ህዝቡ በቤተ ክርስቲያን ተሰብስቦ እግዚኦ እያለ ነው። አለማወቅ የሚባለው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሚባለውን ከሆነ ጸሐፊው ትክክል ነበር። ነገር ግን ችጋርን እና ሞትን መደበቅ በጣም አስቸጋሪ ነውና እያየነው ነው፤ ላስተዋለ ችጋር ያባረራቸውን በአዲስ አበባ መንገዶችም ላይ ያያቸዋል። ይህንን ለማንሣት የተገደድሁት «እየሮጡ የሚታጠቁት ፖለቲከኞችና የትም የማያደርሰው መንገዳቸው» በሚል በአቶ ጌታቸው ረዳ የተጻፈውን ሳነብ በጣም የሚቀራረብ ሀሳብና አስተሳሰብ ስላገኘሁበት ነው።

Read more...
 
እጃችን ለወገኖቻችን የተዘረጋ ይሁን! (ግርማ ካሳ) Print E-mail
User Rating: / 10
PoorBest 
Friday, 20 June 2008 08:12

ግርማ ካሳ ከቺካጎ ( This e-mail address is being protected from spambots, you need JavaScript enabled to view it ) ሰኔ 13 ቀን 2000 ዓ.ም.

 

ከአሥራ አምስት ዓመታት በፊት፣ ስለ ኤድስ ለመነጋገር በተጠራ ስብሰባ ላይ፣ አንዲት የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑ የሕክምና ባለሞያ የተናገሩት አንድ አባባል ነበር። ያኔ ቀሳፊው የኤድስ በሽታ በሚሊዮን የሚቆጠሩትን ገድሎ፣ የሰው ልጆች ቀንደኛ ጠላት ከተባሉት ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ መከከል የተመደበበት ጊዜ ነበር። ይህ በሽታ ከየት እንደመጣና እንዴት ሊስፋፋ እንደቻለ ሃሳብ የሚሰጡ በርካቶች ነበሩ። ታዲያ እኝህ ሴት የትኩረት አቅጣጫው ወዴት ሊሆን እንደሚገባ ለማስረዳት የአንድ ነብርን ምሳሌ አቀረቡ።

በሻሸመኔ አካባቢ፣ “ድንበር የለሽ ሐኪሞች” የተሰኘው ድርጅት በሚያንቀሳቅሰው የእርዳት መስጪያ ማእከል፣አንዲት እናት ልጇን ስታጥብ

Read more...
 
«StartPrev1234567NextEnd»

Page 1 of 7
 

መለከት የኢትዮጵያ ራዲዮ በቫንኩቨር - ካናዳ፣ ቅዳሜ July 7, 2008 7 AM - 8 AM (Pacific Time) ስርጭቱን ይጀምራል። በቀጥታ ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ!