Home መጣጥፍ አስተያየት ኢትዮጵያና ኤርትራ ወደ ሠላም ወይስ ወደ ጦርነት?
ኢትዮጵያና ኤርትራ ወደ ሠላም ወይስ ወደ ጦርነት? Print E-mail
User Rating: / 8
PoorBest 
Articles
Friday, 29 August 2008 22:48
(ትንታኔ)

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ሠላም ለማስከበርና ለማስፈን በሚል በሁለቱ ሀገራት ድንበር መሃከል ሰፍሮ የነበረው የተባበሩት መንግሥታት ሠላም አስከባሪ ቡድን (አንሚ) ባለፈው ሐምሌ 23 ቀን 2000 ዓ.ም. ተልዕኮው መገባደዱን ገልጾ ከሰፈረበት ጥሎ መውጣቱ አይዘነጋም። የአንሚ ውሳኔ በርካቶችን ያሳሰበ ጉዳይ ከመሆኑም በላይ ሁለቱ ሀገራት ወደ ሠላም ወይንስ ወደ ጦርነት ነው የሚያመሩት? የሚል ጥያቄ አስከትሏል።

 

በአጠቃላይ በኢትዮጵያና በኤርትራ መሃከል በ1991 ዓ.ም. የተከሰተውን ጦርነትና ተያያዥ ጉዳዮች አስመልክቶ በሀገር ውስጥ የሚታተመው እንቢልታ ጋዜጣ በቅጽ 1፣ ቁጥር 34 ዕትሙ “ኢትዮጵያና ኤርትራ ወደ ሠላም ወይስ ወደ ጦርነት?” በሚል ርዕስ አንድ ትንታኔ አስነብቧል።

 

በዚሁ ትንታኔው ላይ የኢትዮጵያና የኤርትራ የድንበር ውዝግብ የመፍትሔ መሰናክል በሁለቱም ሀገሮች ላይ የዴሞክራሲያዊ መንግሥታት አለመኖር ነው ወደሚል መደምደሚያ መደረሱን ያትታል። ጋዜጣው የድንበር ኮሚሽኑና የአንሚ ፋይዳ፣ በኤርትራና በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት ይቀሰቀሳል?፣ ኢትዮጵያና ኤርትራ ጤናማ ግንኙነት ሊጀምሩ ይችላሉ? ለሚሉት ወሳኝ ጥያቄዎች የተለያዩ ወገኖችን በማነጋገርና የተለያዩ ጽሑፎችን በማጣቀስ ልዩ ትንታኔ ሰጥቶባቸዋል። (ይህንን ትንታኔ በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!)

 

 
 

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ