Home ዋና ገጽ

መድረክ የልዑካን ቡድኑን ወደ ውጭ ሀገር ሊልክ ነው Print E-mail

ዶ/ር መራራ ጉዲና አሜሪካን ሀገር ገብተዋል

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 10 ቀን 2002 ዓ.ም. March 19, 2010)፦ መድረክ በሚሳተፍበት የመጭው 2002 ዓ.ም. ምርጫ የገንዘብ ማሰባሰብና ከደጋፊዎቹ ጋር ለመወያየት አንድ የልዑካን ቡድን ሊልክ በዝግጅት ላይ መሆኑን የድርጅቱ አመራር አባል ዶ/ር መራራ ጉዲና በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

መኢአድ በአራተኛው ዙር የፓርቲዎች ክርክር ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳተፈ Print E-mail

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 10 ቀን 2002 ዓ.ም. March 19, 2010)፦ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲካሄድበት የቆየው የፓርቲዎች ክርክር አራተኛው ክፍል ዛሬ ዓርብ መጋቢት 10 የተጀመረ ሲሆን፤ በቀደሙት ሦስት የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በክርክሩ ያልተሳተፈው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳታፊ ሆኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ሃሳብን በነፃ የመግለጽ ሽልማት ሥነሥርዓት ተካሄደ Print E-mail

(ከግራ ወደ ቀኝ) አና ኦተርሆልም እና ወ/ሮ ሶፊያ ብርሃነ Ethiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 8 ቀን 2002 ዓ.ም. March 17, 2010)፦ ባለፈው እሁድ መጋቢት 5 ቀን 2002 ዓ.ም. (ማርች 14 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ በተካሄደው የኖርዌይ ደራሲያን ማኅበር ዓመታዊ ጉባዔ ላይ የእ.ኤ.አ. 2009 ሃሳብን በነፃ የመግለጽ ሽልማት ሥነሥርዓት ተካሄደ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ኢትዮጵያዊቷ አሪታ ፍራንክሊን (ዘነበ በቀለ) Print E-mail

ዘነበ በቀለ

ርዕሱ ብዙዎችን ያሳስታል ብዬ አልገምትም። የሁለቱንም ዘፋኞች ሙዚቃ አገናዝቦ መረዳት የሚቻል ነውና። አሪታ በልጅነት ዘመኗ ”ሬሰኩዩሚ” እያለች ያቀነቀነችው ሙዚቃ በአንድ በኩል የሙዚቃው ርዕስ ጭንቀቷን ገላጭ ቢመስልም፤ በሌላ በኩል ደግሞ የድምፅዋን ልክ ያሳየችበት ዕፁብ ድንቅ የሆነ ዜማዋ ነው። ኢትዮጵያዊቷ አሪታ ፍራንከሊን ደግሞ በባህላዊ መንገድ ችግርን አምቆ መያዝ እንጂ ለአደባባይ አስጥቶ ማሳየት የተለመደ አይደለምና ሁሉን ቻይ ሆና መከራዋን የምትገፋው ድምፃዊቷ ማሪቱ ለገሠ ነች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

አርቲስት ሌ/ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ በ79 ዓመቱ አረፈ፣ ሥርዓተ ቀብሩ ተፈፀመ Print E-mail

Artist Sahele Degago's Funeral, 15th March 2010“ሞተዋል” የተባሉት አትሌት ዋሚ ቢራቱ በሌ/ኮሎኔሉ ለቅሶ ላይ ተገኝተዋል

አርቲስት ሌ/ኮሎኔል ሳህሌ ደጋጎ, Sahle DegagoEthiopia Zare (ሰኞ መጋቢት 6 ቀን 2002 ዓ.ም. March 15, 2010)፦ አንጋፋው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋች፣ ገጣሚ፣ የዜማ ደራሲ እና የሙዚቃ አቀናባሪ ሌተናል ኮሎኔል ሣfህሌ ደጋጎ የቀብር ሥነሥርዓት ዛሬ መጋቢት 6 ቀን 2002 ዓ.ም. ከቀኑ በዘጠኝ ሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ ፈረንሣይ ለጋሲዮን በሚገኘው በገነተ-ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ዛሬ ተፈፀመ። ሌ/ኮሎኔል ሣህሌ በ79 ዓመቱ በትናንትናው ዕለት ነበር ያረፈው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የ2002 ምርጫ ቀርቧል፤ ኢህአዲግ ጥበቃውን እያጠናከረ ነው Print E-mail

Ethiopia Zare (ሐሙስ መጋቢት 2 ቀን 2002 ዓ.ም. March 11, 2010)፦ ለምርጫው የሁለት ወር ከ15 ቀናት ዕድሜ ቀርቷል። በአዲስ አበባና በተቀሩት የሀገሪቱ ክፍሎች የኢህአዲግ መንግሥት ልዩ ወታደራዊ የጥበቃ ኃይሎችን እያሰማራ መሆኑ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ቢያንስ ዶሮዋን አንሆንም? Print E-mail

Dorowaኩችዬ - መጋቢት 1 ቀን 2002 ዓ.ም. (ማርች 10 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.)

ሹም መሆን ብዙ ፈተና አለው ወዳጄ! አንዲት አነስተኛ ወረዳ ውስጥ አስተዳዳሪ ሆኖ የተመረጠ ሰው የህዝቡን ተሳትፎ ለማግኘት ቁርጥ ሃሳብ ያደርጋል። የነጋዴው፤ ያስተማሪው፤ የተማሪው፤ የገበሬው በር አልቀረውም። የሁሉንም አንኳኳ። አንዱን ቀን እግሩ ካንድ ገበሬ ቤት ይጥለውና ... 

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ኢንጂንየር ግዛቸውና አቶ ስዬ ወደ መቀሌ ያመራሉ Print E-mail

‘ዘመቻው ተጧጡፎ ቢቀጥልም መድረኩም ሆነ ዓረና ከምርጫው አይወጡም’ አቶ ገብሩ አስራት

Ethiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 1 ቀን 2002 ዓ.ም. March 10, 2010)፦ ኢንጂንየር ግዛቸው እና አቶ ስየ አብርሃ ወደ መቀሌ የሚያመሩት እሁድ መጋቢት 5 ቀን 2002 ዓ.ም. መድረክ በትግራይ በሚያደርገው የምርጫ ቅስቀሳ ላይ ተሳትፎ ለማድረግና በትግራይ ክልል የድርጅታቸውን የምርጫ ሂደት ለመከታተል መሆኑን በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ጠቆሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

በመብራት መቋረጥ ምሬት እየጨመረ ነው Print E-mail
Ethiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 1 ቀን 2002 ዓ.ም. March 10, 2010)፦ የግልገል ግቤ ቁጥር ሁለት ከተመረቀና ሥራ ከጀመረ በሁለት ወራት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በአዲስ አበባ ከተማና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመብራት መቋረጥ ህዝብ እየተማረረ መሆኑ ታወቀ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

አቶ ስየ አብርሃ ለቢቢሲው ዘገባ ምላሽ ሰጡ - ‘ዝም ብዬ አልቀመጥም’ ሲሉ ተደምጠዋል Print E-mail

“ባይጫኑን! ባይገፉን! ጥሩ ነው፤ ከተጫኑን ግን ሁሉን ነገር ይፋ እናወጣዋለን!” አቶ ስየ አብርሃ

Ethiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 1 ቀን 2002 ዓ.ም. March 10, 2010)፦ አቶ ስየ አብርሃ እና ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ አሁንም በመከላከያ ሚኒስትርነትና በፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉት የነበረውን የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ ከመንቀፋቸውም በላይ አቶ ስየ አብርሃ ከፍተኛ ትኩረት ለሳበው የቢቢሲ ዘገባ ምላሽ ሰጥተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 
«StartPrev12345678910NextEnd»

Page 1 of 88
 
Banner

Memorial for Abune Zena Markos