ጥሩነሽ ዲባባ ሁለተኛዋን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. August 22, 2008)፦ ዛሬ በቤጂንግ ኦሎምፒክ በተደረገው የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ርቀት ፍፃሜ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አንደኛ በመውጣት ለራስዋ ሁለተኛውን፣ ለኢትዮጵያ ደግሞ ሦስተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች። አትሌት መሠረት ደፋር ደግሞ ሦስተኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የነኀስ ሜዳሊያ አስገኝታለች።
በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት የጉቦ ቅሌት ድራማ
በጉቦ ቅሌት የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት መዝገብ ቤት ኃላፊ ታሰሩ
Ethiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. August 21, 2008)፦ የ50 ዕድሜ ባለፀጋ የሆኑትና ለ30 ዓመታት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያገለገሉት፣ የፍ/ቤቱ የአስተዳደር ክፍል የመዝገብ ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ታዬ ተኮላ ከአ.አ.ዩ. ተማሪ ላይ 200 ብር ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተያዙ። ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ። የታሪኩ ድራማ እንደሚከተለው ይገኛል ...
ፕ/ር መስፍን እና አቶ አስራት ጣሴ አዲስ አበባ ገቡ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. August 21, 2008)፦ በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የአንድነት ለዴሞክራሰና ለፍትህ ፓርቲን ዓላማ ለኢትዮጵያኖች ሲያስረዱና ከህዝብ ጋር ውይይት ሲያካሂዱ የነበሩት ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም እና አቶ አስራት ጣሴ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ መግባታቸውን ከኢትዮጵያ የደረሰን መረጃ አስረዳ።
ቀነኒሳ በቀለና ሁለት አትሌቶች ለ5 ሺህ ፍፃሜ አለፉ
Ethiopia Zare (ረቡዕ ነኀሴ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. August 20, 2008)፦ ዛሬ በቤጂንግ በሦስት ምድብ በተደረገው የወንዶች 5 ሺህ ሜትር ማጣሪያ የተወዳደሩት ሦስቱም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ውድድሩን በሦስተኝነት በመጨረስ ማጣሪያውን አልፈዋል።
ጥሩነሸ ዲባባ እና ስለሺ ስኅን ከኦሎምፒክ መልስ ይጋባሉ
አትሌት ቀነኒሳ ያሸነፈው የባለቤቱ ስም በተጻፈበት ጫማ ነው
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነኀሴ 13 ቀን 2000 ዓ.ም. August 19, 2008)፦ እጮኛሞቹ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ እና አትሌት ስለሺ ስኅን ከቤጂንጉ ኦሎምፒክ መልስ ሀገር ቤት ጋብቻቸውን እንደሚፈጽሙ ታወቀ። አትሌት ቀነኒሳ 10,000 ሜትሩን የሮጠበት ጫማ ላይ የባለቤቱን ስም አጽፎ ነበር።
የ5 ሺውን የሴቶች ማጣሪያ ሦስቱም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አለፉ
ቅዳሜ የሚደረገው ፍፃሜ በጉጉት ይጠበቃል
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነኀሴ 13 ቀን 2000 ዓ.ም. August 19, 2008)፦ ዛሬ በቤጂንግ ኦሎምፒክ በሁለት ምድብ በተደረገው የሴቶች 5,000 ሜትር ማጣሪያ የተሳተፉት ሦስት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ማጣሪያውን አለፉ።
የብሔር (ጎሣ) ግጭት መንስዔዎችና መፍትሔዎቹ
( ትንታኔ)
ከ81 በላይ የሆኑ ብሔሮች በኢትዮጵያ እንዳሉ ይታወቃል። እነዚህ ብሔር ብሔረሰቦች ለረዥም ዘመናት የቆየና የዳበረ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ ትስስር እንደነበራቸውና እንዳላቸው እሙን ነው። በተቃራኒው ደግሞ በተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች መካከል ግጭቶች ሲከሰቱ ኖረዋል። በተለይ ከ1983 ዓ.ም. የመንግሥት ለውጥ ወዲህ ግጭቶቹ እየበረከቱ ስለመምጣታቸው ብዙዎች ይስማሙበታል።
አንድነት ፓርቲ የዓመት መርሐግብሩ 9 ሚሊዮን ብር ይፈጃል
"ፓርቲው የተጠየቀውን አሟልቶ ለምርጫ ቦርድ አስገብቷል" ወ/ት ብርቱካን
Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 12 ቀን 2000 ዓ.ም. August 18, 2008)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፣ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲን ለማስፈን ለሚያካሂደው ትግል ለማሳካት ዓመታዊ ወጪው ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚፈጅ ዋና ፀሐፊው አቶ አስራት ጣሴ ገለጹ።
”ከማቀርበው ይግባኝ ትክክለኛ ፍትህ እጠብቃለሁ” ካሊድ አደም
Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 11 ቀን 2000 ዓ.ም. August 17, 2008)፦ ”ልጅህን በመቀስ ገርዘሃል” ተብሎ ማርች 28 ቀን 2003 እ.ኤ.አ. በቁጥጥር ስር ውሎ፣ አፕሪል 4 ቀን 2004 እ.ኤ.አ. በ50 ሺህ ዶላር ዋስትና ተለቅቆ ጉዳዩን በፍርድ ቤት ሲከታተል ከቆየ በኋላ ኖቨምበር 2 ቀን 2006 እ.ኤ.አ. የ10 ዓመት ጽኑ እስራት የተፈረደበት ነዋሪነቱ በጆርጂያ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ ኤሜሪካ የሆነው ካሊድ አደም ”ከማይቀርበው ይግባኝ ትክክለኛ ፍትህ እጠብቃለሁ” ሲል ሰሞኑን ደብዳቤ መጻፉ ታወቀ። ሙሉ የደብዳቤው ቃል እንደሚከተለው ይገኛል።
ቀነኒሳ ወርቅ፣ ስለሺ ብር በ10 ሺህ ሜትር አሸነፉ
ቀነኒሳ የራሱን የኦሎምፒክ ክብረወሰን ሰበረ
አጓጊና ልብ አንጠልጣይ ውድድር ነበር

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 11 ቀን 2000 ዓ.ም. August 17, 2008)፦ ዛሬ በቤጂንጉ ኦሎምፒክ በ10 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በራሱ የተይዞ የነበረውን የኦሎምፒክ ክብረወሰን በማሻሻል አንደኛ ሲወጣ፣ አትሌት ስለሺ ስህን ሁለተኛ፣ አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ ደግሞ ስድስተኛ በመውጣት ውድድሩን ጨርሰዋል።
