በጉቦ ተጠርጥሮ የታሰረው የቴሌው ባለሥልጣን ከሀገር እንዳይወጣ ታግዶ በዋስ ተለቀቀ
Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 10 ቀን 2000 ዓ.ም. August 16, 2008)፦ ከቻይናው የቴሌኮምዩኒኬሽን ኩባንያ በሕገወጥ መንገድ ኮሚሽን ለመቀበል ሞክሯል በሚል ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ውሎ የነበረው የኢትዮጵያ ቴሌኮምዩኒኬሽን ኮርፖሬሽን ባለሥልጣን ረቡዕ ነኀሴ 7 ቀን 2000 ዓ.ም. ተረኛ በነበረው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 9ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ በ10 ሺህ ብር ዋስ የተለቀቀና ከሀገር እንዳይወጣ እገዳ የተጣለበት መሆኑ ታወቀ።
ጥሩነሽ ዲባባ የኦሎምፒክ ክብረወሰን በመስበር ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኘች

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 9 ቀን 2000 ዓ.ም. August 15, 2008)፦ በቤጂንጉ ኦሎምፒክ በተደረገው የሴቶች 10 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የኦሎምፒክን ክብረወሰን በመስበር ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች።
እስራኤል ፈላሻ ሙራዎችን መውሰድ አቆመች
Ethiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 8 ቀን 2000 ዓ.ም. August 14, 2008)፦ እስራኤል ላለፉት 30 ዓመታት ከኢትዮጵያ ፈላሻዎችን ወደ ሀገሯ ማጓጓዝ እንዳቆመች ታወቀ። በእስራኤል የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አይሁዶች የእስራኤል መንግሥት የወሰደውን እርምጃ ተቃውመዋል።
ለአለቃ አያሌው ታምሩ መታሰቢያ ድረ ገጽ ተከፈተ
Ethiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 8 ቀን 2000 ዓ.ም. August 14, 2008)፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሊቃውንት ጉባዔ ዋና ሰብሳቢ ለነበሩት ለአለቃ አያሌው ታምሩ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በማሰብና ሥራዎቻቸውን ለምዕመናን ለማቅረብ ሲባል በስማቸው ድረ ገጽ መከፈቱን ልጃቸው ወ/ሮ ጽዮን አያሌው ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ገለጸች።
HR2003'ን በተመለከተ ያሉ ግራ መጋባቶች (ከአማኑኤል ዘሰላም)
የዲፕሎማሲውን እንቅስቃሴ በተመለከተ አስተያየት
ከአማኑኤል ዘሰላም ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ነኀሴ 7 ቀን 2000 ዓ.ም. (August 13, 2008)
በቅድሚያ HR2003'ን በተመለከተ ሃሳብ ከመወርወሬ በፊት በአጭሩ የአሜሪካንን የመንግሥት መዋቅር በአጭሩ ለማሳየት እሞክራለሁ።
አንድነት ከምርጫ ቦርድ ምላሽ ተሰጠው
ቦርዱ የላከው ደብዳቤ ”ለአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ” በሚል ነው
Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 5 ቀን 2000 ዓ.ም. August 11, 2008)፦ ”አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ”ን በምርጫ ቦርድ ለማስመዝገብና ሕጋዊ ፈቃድ ለማግኘት ለቦርዱ ማመልከቻ ያስገቡት የቀድሞው የቅንጅት አመራሮች ጥቂት ማስተካከያዎችን እንዲያሟሉ በድጋሚ ከምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ተገለጸላቸው። ደብዳቤው የተፃፈው ”ለአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ” በሚል መሆኑን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።
"በኢትዮጵያ ረሃብ የለም" ጠ/ሚ/ር መለስ
የታይም መጽሔት ዘጋቢ በአዲስ አበባ ተገኝቶ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር ስለ ወቅታዊ የረሃብና እርዳታ ጉዳዮች ያደረገውን ቃለምልልስ ሙሉ ቃል በዛሬው ዕለት (እሁድ ነኀሴ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. / August 10, 2008) የተነበበውና ሀገር ቤት የሚታተመው ሪፖርተር ጋዜጣ በአማርኛ ተርጉሞ እንደሚከተለው አቅርቦታል።
ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ቦክሰኛ ከኦሎምፒክ ውድድር ውጭ ተደረገ
Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. August 10, 2008)፦ በቤጂንጉ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያ በቦክስ ውድድር በብቸኝነት ያሰለፈችው ቦክሰኛ ሞላ ጌታቸው አምባው በክብደት ምክንያት ከውድድሩ መታገዱን ዓለም አቀፉ የቦክስ ማኅበር አስታወቀ።
ለወጪ ቁጠባ ኢትዮጵያውን አትሌቶች በቤጂንጉ መክፈቻ አልተሳተፉም
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉበትን የጊዜ ሠሌዳና ስለኦሎምፒኩ መረጃዎች ይዘናል
Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. August 10, 2008)፦ ዓርብ ነኀሴ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. (በፈረንጆች 080808) በቻይና ቤጂንግ ኦሎምፒክ የመክፈቻ ስነሥርዓት ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ያልተገኙ ሲሆን፣ የተገኙት አብዛኞቹ የኢህአዴግ ሰዎች መሆናቸውን ለመረዳት ችለናል።
በቡታጅራ በወረዳ ስያሜ በተነሳ ብጥብጥ አራት ሰዎች ቆሰሉ
Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. August 10, 2008)፦ በደቡብ ክልል በቡታጅራ ከተማ በጉራጌ ዞን በሚገኙ ሁለት ወረዳዎች ስያሜ አሰጣጣጥ ጋር በተያያዘ በነዋሪዎችና በፖሊስ መካከል በተነሳ ግጭት አራት ሰው ሲቆስሉ፣ 12 ሰዎች መታሰራቸው ታስረዋል።
