“ለረሃብተኛው ተጨማሪ ዕርዳታ ያስፈልገናል” የመንግሥት ባለሥልጣናት
Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. August 09, 2008)፦ ሐሙስ ዕለት የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አበራ ደሬሣ እና የአደጋና መከላከል ዝግጁነት ኤጀንሲ ዳይሬክተር ስምኦን መቻሌ ለዓለም አቀፍ የሚዲያ ሰዎች በሰጡት መግለጫ የረሃብተኛው ቁጥር መጨመሩንና አስቸኳዋይ የምግብ ዕርዳታ እንደሚስፈልግም ገለጹ።
ሀገረማርያም በተነሳ የጎሣ ግጭት 8 ሰዎች ሞቱ
Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. August 09, 2008)፦ በግጦሽ መሬትና በድንበር ግጭት ምክንያት በተነሳ አለመግባባት በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን በደቡብ ክልል የሚዋሰኑ ከአዲስ አበባ 534 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ሀገረማርያም ከተማ 47 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኙ ሁለት ጎሣዎች መካከል በተነሳ ግጭት ስምንት ሰዎች መሞታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ።
አንድ የኢህአዲግ የፓርላማ አባል እንግሊዝ አገር ጥገኝነት ጠየቀ
Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. August 09, 2008)፦ አቶ በለጠ ኢታና የተባሉ የገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ የፓርላማ አባል እና በፓርላማው የመንግሥት አስተዳዳር ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝዳንት በእንግሊዝ አገር ጥገኝነት መጠየቁ ታወቀ።
የቴዲ አፍሮ ጠበቃ ተፈታ፣ ቴዲ ከጨለማ ቤት ወጣ
Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. August 08, 2008)፦ የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጠበቃ አቶ ሚሊዮን አሰፋ ባለፈው ረቡዕ ሐምሌ 30 ቀን 2000 ዓ.ም. ”ችሎት በመዳፈር” በሚል ለአንድ ወር ከሃያ ቀናት ከተፈረደበት በኋላ በጠቃው አቶ አበባ አሳምን አማካኝነት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ተዘዋዋሪ ችሎት ይግባኝ በማለቱ አቶ ሚሊዮን ዛሬ ማምሻውን መፈታቱን እንዲሁም ቴዲ አፍሮ ደግሞ 27 ቀናት ታስሮ ከነበረበት ጨለማ ቤት እንዲወጣ መደረጉን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጡ።
ከ34 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለድርቅ ተዘፈነ
Ethiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 1 ቀን 2000 ዓ.ም. August 07, 2008)፦ ወጣት ሔኖክ ገብሬ ከኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ በጋራ በመተባበር ”ምንድንነው ምስጢሩ?” በሚል ርዕስ በሀገራችን በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን ድርቅና ረሃብ በሚመለከት ነጠላ ዜማ በዛሬው ዕለት ለህዝብ አቅርቧል።
የጥላቻ-ፖለቲካ ለኢትዮጵያ ህልውና ጠንቅ ነው (ከአብርሃም ያየህ)
ከአብርሃም ያየህ (ሐምሌ 30 ቀን 2000 ዓ.ም. / August 6, 2008)
ባሁኑ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ የቃሚዊው ጎራ፣ የአብዛኛዎቹ ተቃዋሚ ነን ባይ ኃይሎችና ደጋፊዎቻቸው ዋነኛ የማታገያ ስልት ሆኖ በማገልገል ላይ ያለው በጥላቻ የተመሰረተ ፖለቲካ ነው። ይህ መርዘኛና አደገኛ የጥላቻ-ፖለቲካ፣ በትግራይ ስም በሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ወይም በገዢው ፓርቲ ብቻ ያተኮረ አይደለም። አትኩሮቱ፣ በጅምላ አጠቃላዩን የትግራይ ህዝብ ዒላማ ያደረገ ነው። የህዝባቸውና ያገራቸው ህልውና የሚከነክናቸው ዜጎች፣ የዚህ አደገኛ በሽታ መዘዙ በትክክል ተረድተው አጥብቀው ካልታገሉት በቀር፣ ሄዶ-ሄዶ በመጨረሻ ኢትዮጵያን በመበተን ያለው ሚና እጅግ ወሳኝ ነው።
ነገ ኢህአዴግን ልንደግፍ እንችላለን (ግርማ ካሣ)
ግርማ ካሣ (ቺካጎ) This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. - ሐምሌ 30 ቀን 2000 ዓ.ም.
የቅንጅት ወራሽ ነው ብዬ የማምነው፣ መሰረቱን ኢትዮጵያ ያደረገውንና ሠላማዊ በሆነ መንገድ በኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ ለማምጣት እየታገለ ያለውን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ አንደአብዛኛው ኢትዮጵያዊ እደግፋለሁኝ። አንደ አብዛኛው ኢትዮጵያዊም ኢህአዴግን የምቃወም ሰው ነኝ።
የአንድነት ፓርቲ ማመልከቻ ዓርብ በቦርዱ ይታያል
ቦርዱ በአንድ ወር ምላሽ ካልሰጠ ድርጅቱ ሕጋዊ ይሆናል
Ethiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 1 ቀን 2000 ዓ.ም. August 07, 2008)፦ ዛሬ ከአዲስ አበባ በደረሰን መረጃ መሰረት አንድነት ፓርቲ አስር ማስተካከያዎችን አድርጎ ያስገባው ማመልከቻ ከጽሕፈት ቤቱ ወደ ቦርዱ መመራቱንና ዓርብ ለመጀመሪያ ጊዜ ቦርዱ እንደሚያየው ታወቀ።
የቴዲ አፍሮ ጠበቃ እስር ተፈረደበት
ጋዜጠኛው በገደብ ተለቋል
የቴዲ ጠበቃ እንቁጣጣሽን ቃሊቲ ያሳልፋል
Ethiopia Zare (ረቡዕ ሐምሌ 30 ቀን 2000 ዓ.ም. August 06, 2008)፦ የቴዎድሮስ ካሳሁንን ችሎት የሚመሩት ዳኛ ልዑል ገብረማርያም በችሎቱ ሂደት ላይ ፍትሃዊ ባለመሆናቸው የተነሳ ለዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ክስ እመሰርታለሁ በማለት ለአዲስ ነገር ጋዜጣ ላይ ቃለምልልስ የሰጠው የቴዲ አፍሮ ጠበቃና ቃለ ምልልሱን ያተመው ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ዛሬ የተፈረደባቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ዘጋቢዎቻችን አረጋገጡ።
የቴዲ ጠበቃና የአዲስ ነገር አዘጋጅ ለነገ ተቀጠሩ
ታስረው ይቆዩ ተብሏል
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 29 ቀን 2000 ዓ.ም. August 05, 2008)፦ በዳኛ ልዑል ገ/ማርያም ትዕዛዝ ዛሬ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ የታዘዙት የቴዲ አፍሮ ጠበቃ ሚሊዮን አሰፋና የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጅ መስፍን ነጋሽ ታስረው ካደሩበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው፤ ለነገ መቀጠራቸውን የፍርዱን ሂደት ከተከታተሉ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ለማወቅ ችለናል።
