Home ቃለምልልስ
ቃለምልልስ

"በጣም በጥሩ ጤንነት ላይ እገኛለሁ፤ ጥሩ የመንፈሥ መነቃቃት አለኝ" ቴዲ አፍሮ Print E-mail
User Rating: / 60
PoorBest 
Interview

Teddy Afro, ቴዲ አፍሮ ”ግዕዝ ብማር ደስ ይለኛል”

ወጣቱ፣ እውቁና ታዋቂው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ከእስር ከተለቀቀ ሦስት ወር የሆነው ሲሆን፣ በውጭ ሀገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን የመገናኛ ብዙኀን ጋር ሰፋ ያለ ቃለምልልስ ያደረገው ከኢትዮጵያ ዛሬ ድረገጽ ጋር ሲሆን፤ ቃለምልልሱን ያደረገው ከኢትዮጵያ ዛሬ ድረገጽ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ያሬድ ክንፈ ጋር ነው። በዚህ ቃለምልልስ ላይ ያሬድ በቴዲ አፍሮ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ፣ በቴዲ እስር ቤት ቆይታ ላይ፣ በድምፃዊው የሙዚቃ፣ የግጥምና የመድረክ ሥራ ላይ፣ በአርቲስቱ የግል ሕይወት ጉዳይ ላይ፣ ባለፈው ጥቅምት 1 ቀን 2002 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም ለምን ”ያስተሰርያል” የሚለውን ዘፈን እንዳልዘፈነ፣ በስዊድንና በኖርዌይ ኮንሰርቶቹ እሰጥ አገባና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ጥያቄዎችን ለአርቲስት ቴዲ አፍሮ አቀርቦለታል። አርቲስት ቴዲ አፍሮን ለቃለምልልሱ እያመሰገንን፤ መልካም ንባብ ለአንባቢዎቻችን እንመኛለን!

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

“ኢህአዴግ መስቀለኛ መንገድ ላይ የቆመ ፓርቲ ነው” አቶ ስየ አብርሃ (ቃለምልልስ) Print E-mail
User Rating: / 43
PoorBest 
Interview
  • ስለወ/ት ብርቱካንና ስለሌሎች ወገኖቻችን መታሰር ከኢህአዴግ እና ከመንግሥት ጋራ በሚደረግ ድርድር ጉዳዩ መነሣት ይገባዋል
  • በመከላከያ፣ በደኅንነት ፖሊሲዎች እና በተቋማት ግንባታ ዙሪያ የማማከር አገልግሎት ለመስጠት ሥራ ጀምሬያለኹ
  • ኢህአዴግ ነፃነትና ነፃ ምርጫን እንደ ጦር የሚፈራበት ደረጃ ላይ ደርሷል
  • ለኢሠፓ እና ደርግ የበለጠ የሚቀርበው ኢህአዴግ እንጂ ተቃዋሚዎች አይደሉም
  • የኢህአዴግ አመራር ለ30 እና ለ40 ዓመታት በሥልጣን ላይ ለመቆየት ቆርጧል
  • የግል ኑሮዬ በፖለቲካ ጥገኛ እንዲኾን አልፈልግም
  • መጽሐፍ ጽፌያለኹ፤ አቅሙ ከተገኘ በቅርብ ይወጣል

አቶ ስየ አብርሃ (የቀድሞ የመከላከያ ሚንስቴር ሚንስትር)

በሐምሌ ወር 1999 ዓ.ም. ከእስር ከተፈቱ በኋላ አንድ አገራዊ ፕሮጀክት ይዘው እየሠሩ ይገኛሉ። ከቀድሞው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ፕሬዝዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጋራ ስምንት የፖለቲካ ፓርቲዎችን በማቀናጀት “የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ” በተሰኘው ጥምረት ምሥረታ ግንባር ቀደም ተዋናይ ናቸው። እርሳቸው “የጠንካራ ተቃዋሚን ክፍተት የሚሞላ ትልቅ አገራዊ ፕሮጀክት ነው” ይሉታል - ጥምረቱን። ለአንድ ዓመት ከስድስት ወር በምክክር የቆየውን መድረከ ለጥምረት ካደረሱት እና በጥምረቱ ብሥራት ወቅት በታዛቢነት ከተሳተፉት የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስተር ሚኒስትር አቶ ስየ አብርሃ ጋራ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ ሰፋ ያለ ቃለምልልስ አድርጋለች። ቃለምልልሱን እነሆ! መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

“ህዝቡ ያሳየኝን ፍቅር ከፍዬ አልጨርሰውም” ቴዲ አፍሮ Print E-mail
User Rating: / 125
PoorBest 
Interview
Saturday, 15 August 2009 06:21

Exclusive Interview by Tsion Girma

Big mother kiss ከእናቱ ጋራ ሻማ ሊያበራ
 

ከአንድ ዓመት ከአራት ወር እስር በኋላ የተለቀቀው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ የመጀመሪያውን ሰፋ ያለ ቃለምልልስ ከጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ ጋር አድርጓል። ቃለምልልሱ የእስር ቤት ቆይታው ምን ይመስል እንደነበር፣ ጊዜውንስን በምን ሁኔታ ያሳልፍ እንደነበር፣ ምን እንዳጋጠመው፣ አብረውት ታስረው ስለነበሩት እስረኞች፣ ከእስር ነፃ ከሆነ በኋላ የሚኖረውን የሙዚቃ ሕይወት፣ ስለወላጅ እናቱ፣ በፍርዱ ላይ የተሰማውን ስሜት፣ ስለአድናቂዎቹ፣ ስለጠያቂዎቹ፣ ስለግጥሞቹ፣ ስለዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ፣ … በአጠቃላይ ስለባለፉት 484 ቀናት እና ስለወደፊት ዕቅዱ ያስዳስሰናል። መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

”ፀረ-ሽብር ሕጉ ከሕገ-መንግሥቱ በላይ ነው” ጠበቃ ሼክስፒር ፈይሣ Print E-mail
User Rating: / 42
PoorBest 
Interview

ከኢካድ ፎረም ተክለሚካኤል አበበ ከጋዜጠኛ አብርሃ በላይ (የኢትዮ-ሚዲያ) ድረ ገጽ ዋና አዘጋጅ እና ከታዋቂው ጠበቃ ሼክስፒር ፈይሣ ጋር ያደረገው ክፍል ሁለት ቃለምልልስ ነው። የማጫወቻ ቁልፉን በመጫን ይመልከቱ!

 

 

“ህወሓት ፀረ-ኢትዮጵያ ድርጅት ነው፤ መለስ ኢትዮጵያዊ አይደለም” አብርሃ በላይ (የኢትዮ-ሚዲያ ዋና አዘጋጅ) Print E-mail
User Rating: / 76
PoorBest 
Interview

ከኢካድ ፎረም ተክለሚካኤል አበበ የኢትዮ-ሚዲያ ድረ ገጽ ዋና አዘጋጅ ከሆነው ጋዜጠኛ አብርሃ በላይ ጋር ቃለምልልስ አድርጓል። ቃለምልልሱ በተለይም በአቶ ስዬ አብርሃ፣ በህወሓት እና በትግራይ ህዝብ ጉዳይ ዙሪያ ያተኮረ ነው። ጋዜጠኛ አብርሃ በአሁን ሰዓት የትግራይ ህዝብ ህወሓትን እንደማይወደው በቃለምልልሱ ላይ የገለጸ ሲሆን፣ ከፓርቲው ጋር እየሠሩ ያሉትን ሆነ ሲሰሩ የቆዩት ሰዎች “ፀረ-ኢትዮጵያዊ” መሆናቸውንና ፓርቲውም ፀረ-ኢትዮጵያዊ ድርጅት ነው ሲል ገልጿል። ጠ/ሚ መለስ፤ "ኢትዮጵያዊ አይደለም" ይላል ጋዜጠኛ አብርሃ በቃለምልልሱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 
«StartPrev12345NextEnd»

Page 1 of 5
 
Ethiopian-Eritrean Friendship Conference, San Jose March 12-14

Memorial for Abune Zena Markos

በጽሑፍ መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ!

በማናቸውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያየት፣ ትችት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ … በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጽፈው ከራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጽሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻችን 

ethiopiazare@gmail.com ቢልኩልን ለሥራችን ቅልጥፍና ይረዱናል።

ኢትዮጵያ ዛሬ