|
|
|
Saturday, 12 April 2008 09:28 |
|
ከአቶ ዳንኤል በቀለ እና ከአቶ ነፃነት ደምሴ ጋር የተደረገ ቃለምልልስ
Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሚያዝያ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. April 12, 2008)፦ መጋቢት 19 ቀን 2000 ዓ.ም. ከእስር የተፈቱት የሲቪል ማኅበረሰብ መሪዎች አቶ ዳንኤል በቀለ እና አቶ ነፃነት ደምሴ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለእራሳቸው፣ ስለቤተሰቦቻቸው፣ ስጓደኞቻቸው፣ ስለሥራዎቻቸው፣ ስለእስሩ፣ ስለክሱና የፍርድ ሂደቱ፣ … ሀገር ውስጥ ከሚታተመው እንቢልታ ለተሰኘው ሣምንታዊ ጋዜጣ ቃለምልልስ ሰጡ። የአቶ ነፃነት ደምሴ እህት ወ/ት የምሥራች ደምሴ የአቶ ዳንኤል በቀለ እጮኛ እንደሆነችና በቅርቡም ተጋብተው ባለቤቱ እንደምትሆን ከቃለምልልሱ ለመረዳት ተችሏል። ከዚህም ሌላ ክሱን በዋነኛነት ይመራ የነበረውና “በሞት ፍርድ ይቀጡልኝ” እያለ ሲከራከር የነበረው ዓቃቤ ሕግ ሽመልስ ከማል ከአቶ ዳንኤል በቀለ ጋር የ20 ዓመት ጓደኛሞች እንደነበሩ በቃለምልልሱ ላይ ይፋ ሆኗል። አቶ ሽመልስ እና አቶ ዳንኤል ከዩኒቨርስቲ ወደ ሥራ እስከተሰማሩበት ጊዜ ድረስ፣ አንድ ማዕድ አብረው ቆርሰው፣ ያላቸውን ሣንቲም ለሁለት ተካፍለው አብረው በልተውና፣ አብረው ጠጥተው ከኢትዮጵያ እስከ እንግሊዝ አገር ዘልቀው፣ በአንድ አልጋ ላይ ተኝተው፣ የሆድ የሆዳቸውን ያወሩ ጓደኛሞች ነበሩ። ቃለምልልሱን ያደረገችላቸው ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ ስትሆን፤ እንቢልታ ጋዜጣ ያወጣውን ሙሉውን ቃለምልልስ እንደሚከተለው አቀርበነዋል።
|
|
Read more...
|