|
Monday, 05 January 2009 23:46 |
|
Ethiopia Zare (ሰኞ ታህሳስ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. January 05, 2009)፦ ሰኞ ዕለት በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳንና የቴዎድሮስ ካሳሁንን (ቴዲ አፍሮ) አለአግባብ መታሰር፤ እየተፈጸመ ያለውንም ግፍና በደል፤ እንዲሁም የዲሞክራሲ መታፈንን፤ በመቃወም በስቶክሆልም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጽ/ቤት በራፍ ተገኝተው ቁጣቸውን ገለጹ።
|
|
Read more...
|
|
Monday, 05 January 2009 23:41 |
|
የሕትመት ዋጋን በመጨመር ነፃው ፕሬስ ላይ ጥቃት ሊሰነዘር ነው Ethiopia Zare (ሰኞ ታህሳስ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. January 05, 2009)፦ በመንግሥት የሚተዳደረው ብርሃንና ሠላም ማተሚያ ቤት ከጥር አንድ ቀን 2001 ዓ.ም. ጀምሮ በጋዜጦች ላይ የሕትመት ዋጋ የሚጨምር ሲሆን፣ ከምርጫ 97 በኋላ የተቋቋሙት ጥቂት የፕሬስ ውጤቶች ከገበያ እንዲወጡ የሚያደርጋቸው መሆኑ ታወቀ። “ፕሬሱን ለማዳፈን የታለመ ነው” ተብሎ ተተችቷል። |
|
Read more...
|
|
Saturday, 03 January 2009 23:50 |
|
ወ/ት ብርቱካንን መጠየቅ አይቻልም፤ እናትና ልጃቸው ብቻ ተፈቀደላቸው Ethiopia Zare (ቅዳሜ ታህሳስ 25 ቀን 2001 ዓ.ም. January 03, 2009)፦ ቅዳሜ ዕለት ወ/ት ብርቱካንን ቃሊቲ ወሕኒ ቤት ለመጠየቅ የሄዱ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ለረዥም ሰዓታት እንዲጠብቁ ከተደረገ በኋላ ገብተው እንዳይጠይቋቸው ተከለከሉ። የወ/ት ብርቱካን ወላጅ እናትና የአራት ዓመት ሕፃን ልጃቸው ብቻ ለ40 ደቂቃ አገኟቸው። ሕፃንዋ ልጃቸው ከቃሊቲ እስር ቤት ስትወጣ ተንሰቅስቃ አለቀሰች። |
|
Read more...
|
|
Friday, 02 January 2009 21:15 |
|
Ethiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. January 02, 2009)፦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ የፖለቲካ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑትና የ34 ዓመቷ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከታሰሩበት ያለፈው ሰኞ ታህሳስ 20 ጀምሮ ሁለት በሁለት በሆነ ክፍል ውስጥ ለብቻቸው የታሰሩ ሲሆን፣ ላለፉት አምስት ቀናት በረሃብ አድማ ላይ እንደሚገኙ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ጠቆመ። |
|
Read more...
|
|
Friday, 02 January 2009 20:57 |
|
Ethiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. January 02, 2009)፦ አዲሱ የዓባይ ድልድይ በተመረቀ በአራት ወሩ በዚህ በያዝነው ሣምንት ለትራፊክ (ለተሽከርካሪዎች) አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ክፍት መሆኑን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ጠቆመ።
|
|
Read more...
|
|
Friday, 02 January 2009 08:21 |
|
በስዊድን የአንድነት ፓርቲ ድጋፍ ሰጪ ማኅበር መግለጫ አወጣ
Ethiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. January 02, 2009)፦ በስዊድን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የድጋፍ ሰጪ ማኅበር የወ/ት ብርቱካንን መታሰር አስመልክቶ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ ሊቀመንበሯ ካለአንዳች ቅድመ ሁኔታ ከእስር እንዲፈቱ ጠይቋል። |
|
Read more...
|
|
Wednesday, 31 December 2008 09:05 |
|
የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን መታሰር አስመልክቶ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ “የብርቱካን ሚደቅሳ እንደገና መታሰር በሀገራችን እየታየ ያለውን የሕግ ጥሰት አጉልቶ ያሳያል፤ ከሕግ በላይ መሆን ይቁም!” በማለት መግለጫ አውጥቷል። በዚሁ መግለጫው የሊቀመንበሯ መታሰር በሳቸው ላይ ሳይሆን በፓርቲው ላይ ያነጣጠረ ነው ሲል ኮንኖታል። |
|
Read more...
|
|
Monday, 29 December 2008 18:30 |
|
Ethiopia Zare (ሰኞ ታህሳስ 20 ቀን 2001 ዓ.ም. December 29, 2008)፦ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በቅንጅት አመራርነታቸው ወቅት ከተከሰሱበትና ከተፈረደባቸው በኋላ በሽምግልና ቢፈቱም፤ ይቅርታው ተነስቶባቸው ቀድሞ የተፈረደባቸው የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈፃሚ እንዲሆን በማለት ገዥው የኢህአዲግ ፓርቲ ወደ ቃሊቲ እስር ቤት እንደወረወራቸው የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ከአዲስ አበባ አስረዱ።
|
|
Read more...
|
|
Monday, 29 December 2008 15:55 |
|
 ድርጊቱ የተፈጸመው ከፓስተር ዳንኤል ጽ/ቤት ሲወጡ ነው
Ethiopia Zare (ሰኞ ታህሳስ 20 ቀን 2001 ዓ.ም. December 29, 2008)፦ ዛሬ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከሰዓት በኋላ ወደ 8፡30 ሰዓት አካባቢ ቦሌ ከሚገኘውና ከሽማግሌዎቹ አንዱ ከሆኑት ፓስተር ዳንኤል ጽ/ቤት ለአራት ሰዓታት ቆይተው የወጡት የ78 ዓመቱ ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ተደብድበው ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ደግሞ ታስረው ወዴት እንደተወሰዱ ለጊዜው ለማረጋገጥ አልተቻለም። |
|
Read more...
|
|
Sunday, 28 December 2008 23:34 |
|
ስድስት ምሁራን የውይይት ጽሑፋቸውን አቅርበዋል Ethiopia Zare (እሁድ ታህሳስ 19 ቀን 2001 ዓ.ም. December 28, 2008)፦ መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ (የምክክር መድረክ) ቅዳሜ ዕለት በኢምፔሪያል ሆቴል ባዘጋጀው የውይይት ዝግጅት ላይ ስድስት ምሁራን የውይይት ጽሑፍ ማቅረባቸውን ከአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር ዘገበ። |
|
Read more...
|
|
|
|
Page 1 of 41 |