የመስቀል በዓል በጉራጌዎች ዘንድ - ቅዱስ ሃብት በላቸው (ከአውስትራሊያ)
ቅዱስ ሃብት በላቸው (ከአውስትራሊያ)
የመስቀል በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች ዘንድ በደማቅ ሁኔታ ከሚከበሩት አውደ-ዓመቶች አንዱ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
ቅዱስ ሃብት በላቸው (ከአውስትራሊያ)
የመስቀል በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች ዘንድ በደማቅ ሁኔታ ከሚከበሩት አውደ-ዓመቶች አንዱ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
ይመኩ ታምራት ከሎንዶን
መቶ አርባ-አምስት ዓመት ያስቆጠረውን መቅደላን ስናነሳ መቼም ዓፄ ቴዎድሮስና ታላቁ ጀብዷቸው፤ ሮበርት ናፒዬር እና እንግሊዞች በሀገራችን ላይ ያካሄዱት ከ'ግዳጅ ወሲብ' ጋር የማይተናነስ ደፈራ እና ብዝበዛ፣ የነደጃች ካሣ ምርጫ ሴራ፤ የልጅ ዓለማየሁ መሰደድና በለጋ ዕድሜው ከሀገርና ከዘመድ ተለይቶ ሳለ የሕይወቱ በአጭሩ መቀጠፍ፣ ወ.ዘ.ተ. ይታወሱናል። ስለዚያ ወቅት ታሪክ በጥልቀት ለሚያጠና፣ አያሌ መጻሕፍትና ማስታወቻዎች፤ አብዛኞቹ በነጮቹ፣ አንዳንድም በኛው ሰዎች ተጽፈው በታሪክ ማኅደር ውስጥ ይገኛሉ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሣ ጂግሳ
ይድረስ ለተከበሩ ዶ/ር በያና ሱባ፣ የኦሮሞ ዲሞክራሲ ግንባር አመራር አባል በአሉበት።
ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልዎት ያነሳሱኝ ምክንያቶች ርስዎ በቅርቡ ለኢሳት ራዲዮ የሰጡት ቃለመጠይቅ እና አሁን ርስዎ የሚመሩት ከሣምንት በፊት የተቋቋመው "የኦሮሞ ዲሞክራቲክ ግንባር" የወሰዳቸው አቋሞች ናቸው። የርስዎ ቃለመጠይቅና የግንባሩ አዲስ አቋሞች በግሌ እንደአስደሰቱኝ በዚህ አጋጣሚ ልገልጽልዎ እወዳለሁ።
ጋዜጠኛው ኤን. ማንጄላ (N. Mandela) በኢትዮጵያ
ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
በታኅሣሥ አጋማሽ 1954 ዓ.ም በግርማዊ ንጉሠ ነገሥቱ ጥሪ ተደረገለትና በጥር መጀመሪያ ላይ አዲስ አበባ ገባ። ይህ ሰው በሦስት ወራት ከአንድ ሳምንት (በ98 ቀናት) ቆይታው ወቅት እጅግ የተጣበበ መርሐ ግብር እንደነበረበት ያስታውቃል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5
ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
ማንም በዕድሜው ብዛት አያስጠራም ስሙን
በጥቂቱም ዕድሜው ይሠራል ሐውልቱን።
የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
የአድዋው ድል
ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
የዐድዋ ጦርነት እስከዛሬ በአፍሪካም ምድርና በአፍሪካ ታሪክ ከተከናወኑት ጦርነቶች ከፍተኛውን የዋጋና የክብር ድልድል የያዘ ጦርነት ነው። አኒባል የአልፕን ተራሮች ዞሮ የአውሮፓን ኃያል መንግሥት ካሸነፈ ወዲህ፣ አንድ አውሮፓዊ ጦር በአፍሪካውያን ጦር ሲሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ስለሆነም፣ ጦርነቱ ብዙ መልክና ብዙ ቅጽል ተሰጥቶታል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5
(ከየካቲት 8/1929 - የካቲት 17/1929 ዓ.ም)
ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
በመስከረም 1927 ዓ.ም የወጣው Detroit Times — (Sept. 22, 1935, p. 3) መጽሔት ከአንድ ታላቅ ሳይቲስትና የፈጠራ ባለሙያ ጋር የኢትዮጵያንና የጣሊያንን ወረራ አስመልክቶ ቃለ-ምልልስ አድርጎ ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
በ1900 ዓ.ም. በኢትዮጵያና በፈረንሳይ መንግሥታት ስምምነት፣ “በልዩ የቆመ ፍርድ ቤት” የሚል ስያሜ የተቋቋመ ፍርድ ቤት ነበር። ፍርድ ቤቱ የመጀመሪያ ሥራውን በ1914 ዓ.ም. ሲጀምር፣ የመጀመሪያው የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ብላቴን ጌታ ሕሩይ ወልደ ሥላሴ ነበሩ። ከርሳቸውም ቀጥለው የተሾሙትም ነጋድራስ አፈወርቅ ገብረየሱስ ናቸው። የዚህ ፍርድ ቤት ዋነኛው ተግባር የውጭ ዜጎች እርስ-በራሳቸው ሲጋጩና/ወይም የውጭ አገር ዜጎችና ኢትዮጵያውያን በተጋጩ ወይም በተካሰሱ ጊዜ ፍርድ መስጠት ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5
ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ “መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ” (1948) በታተመው መጽሐፋቸው ውስጥ እንደበየኑት፣ “ፊደል ማለት ቀለም፤ ምልክት፤ የድምፅና የቃል መልክ፤ ሥዕል፤ መግለጫ ማስታወቂያ፤” ነው (ገጽ 616)። ደስታ ተክለ ወልድም በበኩላቸው፣ በ1962 ዓ.ም. ባሳተሙት “ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት” መጽሐፋቸው እንደገለጹት፣ “ፊደል ማለት የነገር፣ የቃል ምልክት፣ የድምፅ ሥዕል፣ ማጉሊያ፤ መግለጫ ነው፤” (ገጽ 988)። በሁለቱም ሊቃውንት አተያይ ውስጥ ፊደል የድምፅና የቃል ምልክት መሆኑን በአጽንዖት ተገልጧል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 3 / 5
ካሣሁን ዓለሙ
”ወርቅ ነው፤ ወርቅ ነው የግዕዝ ፊደል፣
ሰባት እጅ የጠራ በሰባት ባሕል።” አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ
የሰውን ልጅ ዕውቀት ታሪካዊ ዕድገት ስንዳስሰው የጽሑፍ ምልክትን በመፍጠር ጀምሮ አሁን ያለንበት የመረጃ ዘመን ላይ ደርሷል። ከጥንቱ የጽሑፍ ምልክት ፈጠራ አንጻር ስንገመግምም በአሁን ጊዜ ያለው የዕውቀት ደረጃ ብዙም ሊለፈፍለት የማይገባ ይመስላል። ምክንያቱም የጥንቱ ለመጀመር የተደረገ ጥረት ነው፤ የአሁኑ ዕውቀት ደግሞ ያለውን ማስፋፋትና ማጎልመስ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...