|
Friday, 04 July 2008 03:03 |
|
የተጭበረበረ ሰነድ እንዲጣራ ለሣምንት ተቀጥሯል ሁለት ጋዜጠኞች ታሰሩ Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 27 ቀን 2000 ዓ.ም. July 4, 2008)፦ ዛሬ ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን እንደሚፈታ በአዲስ አበባ ውስጥ ወሬ ሲናፈስ የሰነበተ ቢሆንም ብይኑ ለሣምንት ተቀጥሯል። በዳግማዊ ምኒሊክ ሆስፒታል ዶ/ር የተፈረመበት የሟች ደጉ ይበልጣል የሞት የምስክር ወረቀት ቴዲ ከተከሰሰበት ቀን ጋር ልዩነት በመፍጠሩ ዳኛው ዛሬ ብይን መስጠት ሲገባቸው እስኪጣራ ለሣምንት ቀጠሮ በመስጠት ችሎቱን መበተናቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።
|
|
Read more...
|
|
Friday, 04 July 2008 01:01 |
|
አሳታሚዎቹ 300 ሺህ ብር መክፈል አለባቸው "ግፊቱ ቢበዛብንም ሀገራችንን ለቀን አንወጣም" ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ "የሚመጣብንን ለመቀበል ዝግጁ ነን" ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 27 ቀን 2000 ዓ.ም. July 4, 2008)፦ ከምርጫ 97 ጋር በተያያዘ ከቅንጅት አመራሮች ጋር ታስረው ድርጅታቸው እንዲፈርስና በገደብ እንዲቀጡ የተወሰነባቸው አራት የጋዜጣ ድርጅቶች ውሳኔው ከተሰጠ ከ11 ወራት በኋላ በቅጣት የተወሰነባቸው ወደ 300 ሺህ ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግሥት እንዲያስገቡ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው ምንጮች ገለፁ። |
|
Read more...
|
|
Thursday, 03 July 2008 13:37 |
|
Ethiopia Zare (ኀሙስ ሰኔ 26 ቀን 2000 ዓ.ም. July 3, 2008)፦ በአንድ ሣምንት ጊዜ ውስጥ የመኖሪያ ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ተነግሯቸው የነበረው የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ተለዋጭ ቤት በኪራይ መልክ ሊሰጣቸው እንደሆነ አስታወቁ።
|
|
Read more...
|
|
Tuesday, 01 July 2008 22:56 |
|
ተጠርጣሪው ጓደኛው ነው Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 25 ቀን 2000 ዓ.ም. July 2, 2008)፦ ወጣት ደጉ ተስፋዬ ሰኔ 13 ቀን 2000 ዓ.ም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን አጠናቅቆ ወደ ቤተሰቦቹ ለመመለስ ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃውን ይዞ፣ ዕቃውን ሸክፎ መናኸሪያ ከደረሰ በኋላ፤ የሞባይል ስልኩ ጠፍቶበት ስለነበር ስልኩ መገኘቱን የሚገልጽ መልዕክት ደርሶት ወደ ግቢው ሲመለስ ነው ሦስት ቦታ በጩቤ ተወግቶ የተገደለው። |
|
Read more...
|
|
Tuesday, 01 July 2008 12:11 |
|
HAPI ከUNESCO እና ከUNOHCHR ጋር በመተባበር ነገ ጠዋት በረቂቅ አዋጁ ላይ ሴሚናር አዘጋጅቶ ነበር Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 24 ቀን 2000 ዓ.ም. July 1, 2008)፦ ከአምስት ዓመት በፊት ኅዳር 25 1995 ዓ.ም. የተረቀቀውና፣ ጥር 5 ቀን 1995 ዓ.ም. (January 13, 2003) ይፋ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ ተቃውሞ የቀረበበትና አፋኝ መሆኑ ሲነገርለት የነበረው አዲሱ የፕሬስ ሕግ ዛሬ በፓርላማው መጽደቁን ለኢትዮጵያ ዛሬ ከአዲስ አበባ የደረሰው መረጃ ጠቆመ። |
|
Read more...
|
|
Monday, 30 June 2008 01:08 |
|
"ግንቦት 7 ንቅናቄን ሊቀላቀሉ ይችላሉ"
Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2000 ዓ.ም. June 30, 2008)፦ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የቀድሞ ፀሐፊ አቶ ሙሉነህ እዩኤል በትናንትናው ዕለት ወደ አሜሪካ ማቅናታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ። |
|
Read more...
|
|
Saturday, 28 June 2008 07:13 |
|
ህዝባዊ ውይይቱ ምን ይመስል ነበር? ያሬድ ክንፈ ከስዊድን ሠላምና ጤናውን ከነቤተሰብህ ያበዛልህ ዘንድ የዘወትር ምኞቴ ነው። ለእመቤትህና ለልጃችሁ የከበረ ሠላምታዬን አቅርብልኝ። ዛሬ የማወጋህ “ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ” የተሰኘውና በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመራው አዲስ ንቅናቄ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከተማ ከህዝብ ጋር ያደረገውን ውይይት ነው። ውይይቱ ቅዳሜ ሰኔ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. እንደሚካሄድ ስላወቅሁ ከስቶክሆልም 220 ኪሎ ሜትር ርቄ ከምኖርበት ሳንድቪከን ከተማ ወደዚያው አመራሁ። ንቅናቄውን በመወከል ዶ/ር ብርሃኑ እና አቶ ቸኮል ጌታሁን ነበር የተገኙት። አቶ ቸኮል የቀድሞው ቅንጅት የላዕላይ ምክር ቤት አባል የነበረ ሲሆን፣ አሁን በስዊድን ስደተኛ ነው። |
|
Read more...
|
|
Friday, 27 June 2008 13:01 |
|
አዲሱ/ተለጣፊው መምህራን ማኅበር የ12 ሚሊዮን ብር ሊወርስ ነው
Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 20 ቀን 2000 ዓ.ም. June 27, 2008)፦ ለሰላሳ ዘጠኝ ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ ሲንቀሳቀስና በአንድ ወቅት በዶ/ር ታዬ ወ/ሠማያት ይመራ የነበረው አንጋፋው የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ከ15 ዓመታት የፍርድ ቤት ሙግት በኋላ ለመጨረሻ ጊዜ በሰበር ችሎት እንዲዘጋ ተወሰነ። አዲሱ/ተለጣፊው የመምህራን ማኅበር ወደ 12 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ወራሽ ሊሆን ነው። |
|
Read more...
|
|
|
|
Page 1 of 25 |