ዋና ገጽ
 

የህዝብ እና የተቃዋሚ ፓርቲዎች መንታ መንገድ Print E-mail

ተመስገን ደሳለኝ

የመኢአድ ም/ሊቀመንበር ዶ/ር ታዲዮስ ቦጋለ የመኢአድ ሊቀመንበር በሆኑት ኢንጂነር ኃይሉ ሻወል በተከሰሱበት ክስ ሁለት አመት ከስድስት ወር ተፈርዶባቸው ከርቸሌ ገቡ፤ መኢአድ እንደአንባሻ ተከፋፈለ፤ የማይለያዩት ኃይሉ ሻውል እና ማሙሸት አማረ ተለያዩ። አንድነት ፓርቲ ብርቱካን ሚደቅሳ ትፈታ ይል የነበረውን ጥያቄ አንዱአለም አራጌ ይፈታ በሚል ቀየረው፤ ብርቱካንን በማስብ ይበራ የነበረውንም ሻማ አንዷአለምን በማሰብ ይበራ ዘንድ ወሰነ፤ ብርቱካን ሚደቅሳ ስለኢትዮጵያ ፖለቲካ ልታጠና ዋሽንግተን ሄደች፣ ስዬ አብርሃ ለትምህርት ወደአሜሪካ ሄዱ፤ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጀርመናዊ ህፃናቶችን ስለኢትዮጵያ ፖለቲካ ሊያስተምሩ ጀርመን ገቡ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ታሪክ ያላነበቡ ታሪክ ሰሪዎችና፣ ታሪክ ያላነበቡት ታሪክ ዘካሪዎች፣ ጉድ አፈሉብን! Print E-mail

ሰሎሞን ተሰማ ጂ. (ከአ.አ) - (ለፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም በተለይ)

0. መግቢያ

ፍሬድርክ ኒቼ በደስታና በፈንጠዝያ የምፎልሉትን እንሰሳት ተጠጋና ጠየቃቸው። "ለምንድነው እንደዚህ ደስተኛ ልትሆኑ የቻላችሁት?" የሚል ነበር ጥያቄው። እነሱም ባንድነት፣ ባንድ ቃል መለሱለት። ምንም ሳይወያዩ፣ ምንም ነገር ሳይፎካከሩ፣ መንፍሳቸውም ሳይቀናና፣ አንዱም ሌላውን ሳይተች፣ ደመ-ነሳቸው በሚነግራቸው መሰረት፣ "ምንም ታሪክ (memory of things) ስለሌለን ነዋ!" አሉት። ከአፍታ በሁዋላ "ምን አላችሁኝ? እስኪ ድገሙልኝ?" ሲል ጥያቄዎቹን አጅጎደጎደባቸው። እነሱ ግን የሰጡት መልስ አጭርና አስገራሚ ነበር። "ምኑን ነው የምንደግምልህ?" የሚልና ክው አድርጎ የሚያስቀር መልስ። ሁሌም የሚደንቀኝ አይነት፣ "ቅስም-ሰባሪ" መልስ ይሉዋችሁዋል እንዲህ ያለው ነው-እንጂ! ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ክርስቲያኑ ማህበረሰብ ከሙስሊሙ ጋር እንዲተባበር ጥሪ ቀረበ Print E-mail

እስላሙም ወገናችን ክርስቲያኑን በመደገፍ፤ ክርስቲያኑም ወገናችን እስላሙን በመደገፍ ሁሉም እንዲነሳና ድምጹን እንዲያሰማ ጥሪየን አቀርባለሁ” ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መልከጸዲቅ

33ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅዱስ ሲኖዶስ ጠቅላላ ጉባኤ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 4 ቀን 2004 ዓ.ም. May 12, 2012)፦ በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሀፊ የሆኑት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መልከጸዲቅ በእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ እደረሰ ያለውን አስከፊ ጭፍጨፋ በማውገዝ መላ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ተከታዮች ከሙስሊሙ ማህበረሰብ ጎን እንዲቆም ጥሪ አስተላለፉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

መለስ ዜናዊ "የአፍሪካ መሪዎች ሙስና ውስጥ የምንገባው በስግብግብ ኩባንያዎች ጫና ነው" አሉ Print E-mail

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 4 ቀን 2004 ዓ.ም. May 12, 2012)፦ ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ የአፍሪካ መሪዎች ሙስና ውስጥ የሚዘፈቁት በወጉ የተደራጁ የውጪ ኩባንያዎች የሚያደርሱትን ጫና ለመቋቋም ስለሚያዳግታቸው መሆኑን አመላከቱ። አቶ መለስ ይህን እምነታቸውን የገለጹት በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ለመምከር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው ወርልድ ኢኮኖሚክ ፎረም ላይ ትላንት (ሐሙስ ግንቦት 2 ቀን) ከአንዲት የፎረሙ ተካፋይ ከሆነች ደቡብ አፍሪካዊት ለቀረበ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የሹክሹክታው ክፍል ሁለት ገፅታ Print E-mail

ተመስገን ደሳለኝ
ከዚህ ቀደም ‹‹ሹክሹክታው ምንድርነው?›› በሚል ርዕሰ ጉዳይ አንድ ፅሁፍ ፅፌ ነበር። የፅሁፉ ጭብጥ የሚያጠነጥነው የአረብ ሀገራት የተሳካ አብዮትን ተከትሎ በኢትዮጵያም ሁለት ዓይነት ሹክሹክታዎች ነፍስ መዝራታቸው ላይ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

በብራስልስ የአውሮፓ ኮሚሽን የተቃውሞ ሰልፍ ተጠራ Print E-mail
  • የኢትዮጵያ መንግሥት በዜጎቹ ላይ እያደረሰ ያለውን የመብት ረገጣ እና እስራት በአስቸኳይ ያቁም!!
  • በኃይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባቱን እና ዜጎችን ማፈናቀሉን ያቁም!!

Ethiopia Zare (ሐሙስ ግንቦት 2 ቀን 2004 ዓ.ም. May 10, 2012)፦”መብታችን ይከበር!” በሚል በኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተጀመረውን እንቅስቃሴ በመደገፍና ”የኢህአዴግ መንግሥት በዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን የመብት ረገጣ፣ እስራት፣ በኃይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባቱንና ዜጎችን ማፈናቀሉን ያቁም!” በሚል መሪ መፈክር የፊታችን ሜይ 16 ቀን 2012 በብራስልስ የአውሮፓ ኮሚሽን ሕንፃ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ ተጠራ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የዋልድባ ገዳም ይዞታና የመነኮሳቱ ሰብዓዊ መብት እንዲከበር ተጠየቀ Print E-mail

ለአቶ መለስ ዜናዊ (የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር - አዲስ አበባ)

ጉዳዩ፦ ታሪካዊ የዋልድባ ገዳማችን ይዞታና የመነኮሳት ሰብዓዊ መብት እንዲከበርልን ስለመጠየቅ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ታሪክ ማኅበራዊና ሥነ- ጥበብ እድገት ያበረከተችው አስተዋጽዖ ከኢትዮጵያ አልፎ በመላው ዓለም የሚታወቅ እውነታ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

በፍትሕ ጋዜጣ ላይ ለምንጽፍ ሁሉ እየተናገሩ አለማነጋገር፣ እያሰቡ አለማሳሰብ Print E-mail

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

ይህ ጽሑፍ ለእኔም የተጻፈ በመሆኑ አንድ ቀልድ እንደመግቢያ ልናገር፤ አማኑኤል ሆስፒታል ሕመምተኛው ውጭ ይጽፋል፤ ሀኪሙ ይመጣና ‹‹ከበደ፣ እንደምናደርህ?›› ብሎት ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ፣ ሀኪሙ ምን እየጻፍክ ነው? ይልና ይጠይቃል፤ ህመምተኛው ‹‹ደብዳቤ›› ይላል፤ ሀኪሙ ‹‹ለማን ነው?›› ብሎ ሲጠይቅ፣ ሕመምተኛው ‹‹ለራሴ›› ይላል፤ ሀኪሙ የሕመምተኛውን የውስጥ ስሜት ለማወቅ ጓጉቶ ‹‹ምን ይላል?›› ብሎ ይጠይቃል፤ ሕመምተኛው በመደነቅ ዓይኑን በልጠጥ አድርጎ ‹‹ዶክተር መቼ ተላከና፣ መቼ ደረሰኝና!›› አለው፤ እኔም…

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የልማት ሠራዊት የሀገሪቱን አንጡራ ሀብት ሲያባክን Print E-mail

ኢንጂነር አብደልወሃብ ቡሽራ - መGለ

በትግራይ ክልል የልማት ሠራዊት እንዲሆኑ ተብለው የተመደቡ አካላት የወረዳና የቀበሌ አስተዳዳሪዎች በሕወሓት ካድሬ መሪነት ነው እሚንቀሳቀሱት። የታዘዙትን የሚፈጽሙ ናቸው። እነዚህ አካላት የተሰማሩበት የሥራ ዓላማ በገጠር በተመረጡ ቦታዎች በመስኖ የሚለማ ግብርና ማፋጠን የሚል ነው። ለዚህ ተብሎ የታቀደው የልማት አቅጣጫ ደግሞ በተመረጡ የገጠር መንደሮች እያንዳንዱን ገበሬ በእርሻ ማሣው የውሃ ጉድጓድ መቆፈር እንዳለበት ነው። በተጨማሪ ከደደቢት የብድር ተቋም የውሃ ሞተር በብድር መልክ በመውሰድ ከጉድጓድ ውሃ እየመጠጠ ወደ እርሻ ማሳ እንዲጠያሰራጭ ታስቦ ነው። ለዚህ ጉዳይ የተመደበው ባጀት እንደሚከተለው ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 

ኤፍሬም ማዴቦ የረሳት ሞገደኛዋ ሚስት Print E-mail

ነጻነት ዘገዬ

ባልና ሚስት ነበሩ። ሚስት ጣም እልኸኛ ናት። ባልዬው ታጋሽ ነው። እርሱዋ ሁል ጊዜ ተቃራኒ ናት። ባልዬው እንብላ ሲላት እስዋ እንሂድ ትላለች፤ እንሂድ ሲላት እንቀመጥ ትላለች፤ በዚህ መልክ እየተዳረቁ ይኖራሉ - ኑሮ ካሉት መቃብርም እንደመሞቁ። በአንድ አጋጣሚ አሳድሩኝ ባይ አንድ የወንድ እንግዳ ወደቤታቸው ይመጣል። ይሄኔ የሚስቱን ጠባይ የዘነጋ ባል ምን ይላል፤ ‹እኔና እንግዶ መደቡ ላይ እንተኛለን፤ አንቺ ከልጆችሽ ጋር እግገኑ ላይ (የገጠር ቤት ሣሎን ማለት ነው) አንጥፋችሁ ተኙ›። ሚስት ሆይት ባል ተናግሮ ሳይጨርስ ካፉ ቀለብ ታደርግና ‹ እንዴት ተደርጎ? ሞኝህን ፈልግ! አንተና ልጆችህ እግገኑ ላይ እኔና እንግዶ እመደቡ ላይ ነው እምንተኛ› ትልና ዘራፍ ትላለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...
 
«StartPrev12345678910NextEnd»

Page 1 of 138

አዲስ ዜናዎችና ጽሑፎች

 
Banner