|
ሰሎሞን ተሰማ ጂ. (ከአ.አ) - (ለፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም በተለይ)
0. መግቢያ
ፍሬድርክ ኒቼ በደስታና በፈንጠዝያ የምፎልሉትን እንሰሳት ተጠጋና ጠየቃቸው። "ለምንድነው እንደዚህ ደስተኛ ልትሆኑ የቻላችሁት?" የሚል ነበር ጥያቄው። እነሱም ባንድነት፣ ባንድ ቃል መለሱለት። ምንም ሳይወያዩ፣ ምንም ነገር ሳይፎካከሩ፣ መንፍሳቸውም ሳይቀናና፣ አንዱም ሌላውን ሳይተች፣ ደመ-ነሳቸው በሚነግራቸው መሰረት፣ "ምንም ታሪክ (memory of things) ስለሌለን ነዋ!" አሉት። ከአፍታ በሁዋላ "ምን አላችሁኝ? እስኪ ድገሙልኝ?" ሲል ጥያቄዎቹን አጅጎደጎደባቸው። እነሱ ግን የሰጡት መልስ አጭርና አስገራሚ ነበር። "ምኑን ነው የምንደግምልህ?" የሚልና ክው አድርጎ የሚያስቀር መልስ። ሁሌም የሚደንቀኝ አይነት፣ "ቅስም-ሰባሪ" መልስ ይሉዋችሁዋል እንዲህ ያለው ነው-እንጂ! ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?
|
|
ሙሉውን አስነብበኝ ...
|