ቁጥር ፩

አሁንስ በዛ የኔ ችግር

መነጽር ፍለጋ ሌላ መነጽር

ይህስ አልመሰለኝም የዓይን

ሰውሮኝ ነው ህሊናዬን

ቁጥር ፪

መሄጃ መች አጣሁ ወደሷማ

ሞልቶኛል ብዙ ጫማ

አልገባችሁም ነገሩ

ተሸፋፍኖ ነው ፍቅሩ።

ቁጥር ፫

እገደል አፋፍ ዛፍ በቅሎ

ለቆረጣ አልመች ብሎ

ዘመድ አዝማድ በአንድነት

እንክበደው ብሎ ወጣበት

ዛፉ ተገንድሶ ወደቀ

የ‘ንክበደው ዘርም አለቀ

ቁጥር ፬

ለምን ትላለህ ሰው ጠፋኝ

መጀመሪያ እራስህን አግኝ

አንተን አግኝተህ ስታበቃ

ሌላ ሰው ፈልግ በቃ።

ቁጥር ፭

እኔ ክፉ ሆንኩ በል ወንድሜ

እኔን አትጥራኝ አለስሜ

ሰው ከፋ ብለህ ጠልተከኝ

ከኔ ፍቅር አትመኝ።

ቁጥር ፮

ሲበርደን ኡ ኡ ታ

ሲሞቀን ኡ ኡ ታ

ሲርበን ኡ ኡ ታ

ስንጠግብ ኡ ኡ ታ

ስንጠማ ጩኸት

ስንጠጣ ጩኸት

ስንፋቀር ጩኸት

ስንጣላ ጩኸት

በድለንም ለቅሶ

ሲበድሉን ለቅሶ

ግራ ግብት አለው

እግዜሩ ጨርሶ


ወለላዬ ከስዊድን (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ