የሕወሓት ሽኩቻ አላባራም!

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive
Azeb Mesfin

“ሃፍታም ምሆነው ሕወሓት ሲለቅቀኝ ነው!" አዜብ መስፍን

ክንፉ አሰፋ

"ሃፍታም የምትሆነው ሕወሓት ወይንም ኤፈርት ሲለቅቀኝ ብቻ ነው!" ብላ ከነገረችን ገና መንፈቅ እንኳ አልሞላም። ከጥልቅ ተሃድሶ እና ከመተካካት ቀጥሎ የተመሰከረለት የአዜብ ጎላ መሪ ቃል ነበረች። የመልቀቁን ጨዋታ ለኛ ተየት አድርጊያትና መሪርዋን ጽዋ ተጎንጪ ሲሉ እነሆ መርዶውን ነግረዋታል። ሂስዋን አልውጥም ብላ ከመቀሌ እንደፈረጠጠች በዚያው ቀርታለች። መቼም "መለስ የሞተው አሁን ነው!" ሳትል አትቀርም በልብዋ። የዛሚዋ ደላሊት እድል አትሰጣትም እንጂ፣ ይህንኑ የልብዋን ሃሳብ "ለሚወዳት ሕዝብ" ትተነፍሰው ነበር። ግን ምን ያደርጋል? የወደቀ ፈላጊ አይኖረውም። ቀልደኛይቱ የጎላ ልጅ፣ "ድሮስ ቢሆን ድሃን ማን ይወደዋል" ማለትዋ በፌዝ ቡክ ላይ አነበብን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በ'ርግጥ በኢትዮጵያ ሕዝብ መኻል ጥላቻ፣ በደልና ቂም በቀል አለ?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active
President of Oromia Regional State, Mr. Lemma Megersa.

ፊልጶስ

የትላንቱ እንቅፋት፣ ዛሬም ይመታናል

የትላንቱ ገመድ፣ ዛሬም ይጠልፈናል፤

ሰምተንም - አልሰማን፣ ሳሰማም ሰምተናል

ዓይተንም - ዓላየን፣ ሳናይም ዓይተናል

ላለመማር - መማር እኛ ተምረናል።

አሁን … አሁን ”ከልሂቃኑ እስከ ኢ-ልሂቃኑ” ድረስ፤ ቀድም ብሎ ሙሰላዊያንና ሂተለራዊያን፤ ካለፉት ሃምሳ ዓመታት ወዲህ ደግሞ ሻዕቢያውያንና ወያኔያዊያን እንዲሁም ኦነጋውያን ከባንዳ አያቶቻቸውና አባቶቻቸው የተቀበሉትን የፈጠራና የጥላቻ ታሪክ ስላወሩትና የሥልጣን ኮርቻውን ስለተፈናጠጡት፤ የሚንናገሩትና የሚጽፉት ሁሉ እንድ ዕውነት ተቆጥሮ፤ “በኢትዮጵያ ሕዝብ መኻል ጥላቻ፣ በደልና ቂም-በቀል አለ!” መባሉ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጓዱን ሬሳ በትግል ሜዳ ጥሎ የሚሮጥ ሥነልቦናና ማኅበራዊ እሴት የወረሰው ኃይል ድልን ሊጨብጣት ይችላልን?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active
Ethiopian opposition leaders

ሸንቁጥ አየለ

ኢትዮጵያ ተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ መሳተፍም ሆነ ሐሳብ መሰንዘር አጸያፊ ሆኖ የሚገኝበት ወቅት ቢኖር የተጋድሎ ጓዳቸውን እሬሳ እንኳን ሊሰበስቡ በሕይወት ያሉ አመራሮቻቸውን የሚረሱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በፍጥነት እየተገነቡ የሚፈርሱበት አገር መሆኑ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጦርነቱ የአፍሪካውያን ሳይሆን የአሜሪካና የአውሮፓ ጦርነት ነው!

የአንባብያን ድምፅ: 3 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar InactiveStar Inactive
ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ

ሻለቃ ዳዊት በቅርቡ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ስለሚካሄደው ጦርነትና ስለኢኮኖሚ ዕድገት ለሰጠው ሐተታ መልስ

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

መግቢያ

ሻለቃ ዳዊት ብቻ ሳይሆን እንደሱ ተመሳሳይ አስተሳሰብ ያላቸው ምሁራን በተለያየ ወቅት የዓለም አቀፍንም ሆነ የአገራችንን ፖለቲካ በሚመለከት በጽሑፍ መልክ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ። በአቀራረባቸውም አንዳንድ የዋህ ኢትዮጵያውያንን ቀልብ የሳቡና አገር ወዳድ ኢትዮጵያውን ናቸው እስከማለት አድርሷቸዋል። ይሁንና አንባቢው እነዚህ ምሁራን የሚሰጡትን አስተያየትና ሐተታ ለመረዳት የፍልስፍናቸውን፣ የቲዎሪዎቻቸውንና የሳይንሳቸውን መሰረት ይጠይቅ አይጠይቅ እንደሆን ለማወቅ አስቸጋሪ ነው። አብዛኛውን ጊዜ አንዳንድ ጽሑፎች በጥሩ የእንግሊዘኛም ሆነ የአማርኛ ቋንቋ ተጠናቅረው በሚቀርቡበት ጊዜ አንባቢው የይዘታቸውንና የሐተታዎችን የኢንፎርሜሼን ምንጭ ሳይመረምር ዝም ብሎ በመቀበል ትክክል ናቸው ብሎ ይደመድማል። እንደምከታተለው ከሆነ አብዛኛዎቹ አንባቢዎች እንደዚህ ዐይነቱን የሻለቃ ዳዊትን የመሳሰሉ ጽሑፎች ውስጣዊ ይዘት ለመመርመርና በተመሳሳይ አርዕስት ላይ ከሚጽፉ፣ ይሁንና ደግሞ በተለየ መልክ ከሚያቀርቡ ሰዎች ጋር የማወዳደር ጊዜና ገት ስለሌላቸው ከአንድ ወገን ብቻ የሚመጣውን ኢንፎርሜሽን አንብበው ትክክል ነው ብለው በመቀበል አላስፈላጊ ድምደማ ላይ ይደርሳሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፖለቲካውን ምስቅልቅል ተረድተህ ጽንፈኛ፣ ቁርጠኛ ብሎም ጦረኛ እስክትሆን፤ አገርና ሕዝብ ከቶም አይኖርህም

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive
ዐፄ ቴዎድሮስ

ሸንቁጥ አየለ

የፖለቲካው ምስቅልቅል

አሁን ያለው የፖለቲካ ምስቅልቅል እውነትና ገጽታው ምን ይመስላል?የጠላት አቋሙስ ምን ይመስላል? ወያኔ ምን እየሰራች ነው? አጠቃላይ የፖለቲካው ትርምስምሱ እንዴት ይገለጻል ብለህ እራስህን ጠይቅ። ከአንድ እስከ አስር ያሉትን ነጥቦች አንድ በአንድ በስፋት እያብራራህ ከእውነተኛ የትግል አጋሮችህ ጋር ብቻ እጅግ ጥልቅ ውይይት አድርግባቸው። እዚህ በደምሳሳው የተሰጡትን ነጥቦች በምሳሌ እያሰፋፋህ የፖለቲካውን ምስቅልቅል መጀመሪያ አጥብቀህ ተረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኦቦ ለማን ያናገራቸው እምነት ወይንስ ስሜት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active
Lemma Megersa

ይገረም አለሙ

የኦሮምያ ክልል ፕሬዝዳንት ለማ መገርሳ ባህር ዳር ተገኝተው ከተናገሩት መካከል ”ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው” የሚለው አስደማሚ ቃል የሚገኝበትን ክፍል በጨረፍታ የሰማሁት ከአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ የአማርኛው ክፍል ነው። ሰምቼ ሳልጨርስ ስሜቴ ተለዋወጠ፣ ለራሴም ልረዳው ባልቻልኩ ሁኔታ የለቅሶ ስሜትም ተሰማኝ። በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኜ ፈጥነው ወደ አዕምሮዬ የመጡት አይታክቴው አባት ምሁር ፕ/ር መስፍን ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ