የሕወሓት ሽኩቻ አላባራም!
“ሃፍታም ምሆነው ሕወሓት ሲለቅቀኝ ነው!" አዜብ መስፍን
ክንፉ አሰፋ
"ሃፍታም የምትሆነው ሕወሓት ወይንም ኤፈርት ሲለቅቀኝ ብቻ ነው!" ብላ ከነገረችን ገና መንፈቅ እንኳ አልሞላም። ከጥልቅ ተሃድሶ እና ከመተካካት ቀጥሎ የተመሰከረለት የአዜብ ጎላ መሪ ቃል ነበረች። የመልቀቁን ጨዋታ ለኛ ተየት አድርጊያትና መሪርዋን ጽዋ ተጎንጪ ሲሉ እነሆ መርዶውን ነግረዋታል። ሂስዋን አልውጥም ብላ ከመቀሌ እንደፈረጠጠች በዚያው ቀርታለች። መቼም "መለስ የሞተው አሁን ነው!" ሳትል አትቀርም በልብዋ። የዛሚዋ ደላሊት እድል አትሰጣትም እንጂ፣ ይህንኑ የልብዋን ሃሳብ "ለሚወዳት ሕዝብ" ትተነፍሰው ነበር። ግን ምን ያደርጋል? የወደቀ ፈላጊ አይኖረውም። ቀልደኛይቱ የጎላ ልጅ፣ "ድሮስ ቢሆን ድሃን ማን ይወደዋል" ማለትዋ በፌዝ ቡክ ላይ አነበብን።
ሙሉውን አስነብበኝ ...