መንግሥት የዜጐችን ደህንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን ይወጣ!! (ኢሰመጉ)
መንግሥት የዜጐችን ደህንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን ይወጣ!!
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ)
ETHIOPIAN HUMAN RIGHTS COUNCIL
ጋዜጣዊ መግለጫ
ጥቅምት 17 ቀን 2012 ዓ/ም
የኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት ክፍል አንድ አንቀፅ 14 ማንኛውም ሰው ሰብዓዊ በመሆኑ የማይደፈርና የማይገሠሥ፣ በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነትና የነጻነት መብት እንዳለው ይደነግጋል፡፡ ማንኛውም ሰው በሕይወት የመኖር መብት እንዳለውና በሕግ በተደነገገ ከባድ የወንጀል ቅጣት ካልሆነ በስተቀር ሕይወቱን እንደማያጣ በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 15 ላይ ሠፍሯል፡፡ የሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 32(1) ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወይም በሕጋዊ መንገድ አገሪቱ ውስጥ የሚገኝ የውጭ ዜጋ በመረጠው የአገሪቱ አካባቢ የመዘዋወርና የመኖሪያ ቦታ የመመሥረት መብት እንዳለው በግልጽ አስቀምጧል፡፡ እንደዚሁም፣ አንቀፅ 40 (1) ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የግል ንብረት ባለቤትነት መብት አጎናጽፏል፡፡
ሙሉውን አስነብበኝ ...



