የረቡዕ ግጥም ፬ኛ ዓመት፣ ቁ. ፳፯
ለምን ብለን
ውሸትን ቻል አ'ርገን
እንደ እርጎ ተግተን
እንደ ሱረት ምገን
ዝም ብለን ምናልፈው
ባለሥጣንን ነው
ፈርተን አጎብድደን
አንድም ለሆድ ብለን
ሙሉውን አስነብበኝ ...ውሸትን ቻል አ'ርገን
እንደ እርጎ ተግተን
እንደ ሱረት ምገን
ዝም ብለን ምናልፈው
ባለሥጣንን ነው
ፈርተን አጎብድደን
አንድም ለሆድ ብለን
ሙሉውን አስነብበኝ ...ፍቅርን ነበረ ይጓዛል እስከሞት
ብለን የምናውቀው ያነበብነው በፊት
ውሸትም እስከሞት ለካ አብሮ ይጓዛል
እንዲህ ያለ ተአምር በዚህ ዘመን ታይቷል
ሙሉውን አስነብበኝ ...ይኼ ኑሮ የምንለው
ሁለት ዐይነት ገጽታ አለው
አንድ ለ'ራስ
ለመንተራስ
አንድ ለአገር
ለመማገር
ሙሉውን አስነብበኝ ...ወለላዬ ከስዊድን
“አዎን! ኢትዮጵያዊ ነኝ!” በለኝ
መቼም አፍህ ከተግባርህ አይከብደኝም
ካልኾንክም ግድ የለም
እቅጩን ሐቁን ንገረኝ
ያንተ ነገር ቁርጡ ይግባኝ።
የኔነቴን የአገሬን ትዝታ
የቀዬው የአድባሩን ሽታ
የፍቅሬን የአንድነት ጥላ
ለዘመናት ያኖረኝን ከለላ
ወዲያ ጥለኸው ሰባብረህ
ከናት ካባትህ ቃል ኪዳን ርቀህ
እንዲህ ኾነህ ያገኘሁህ
ማነህ?
እውነት አንተም ኢትዮጵያዊ ነህ?!
ሙሉውን አስነብበኝ ...ሰኔ ከሰኞ ጋር ገጠመ አልገጠመ
እማይመጣው መጥቶ ሚመጣው መቼ ቆመ
አሥሩ ቢወራ በዛ በዚህ ቢባል
የማይኾን አይኾንም የሚኾን ይኾናል
ሙሉውን አስነብበኝ ...