የሶማሌ ክልል የመራጮች ምዝገባን በተመለከተ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

ኦብነግ፣ ነፃነት እና እኩልነት፣ ኢዜማ እና የግል እጩ ተወዳዳሪዎች ለቦርዱ አቤቱታዎች አቅርበዋል
ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ 2013 የመራጮች ምዝገባ ሒደት ላይ ከፍተኛ አቤቱታ የቀረበበት በሶማሌ ክልል እየተከናወነ ያለው የመራጮች ምዝገባ ሒደት ነው። በዚህ ሒደት ላይ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ለቦርዱ አቤቲታዎችን ያቀረቡ ሲሆን፤ (ኦብነግ፣ ነፃነት እና እኩልነት፣ ኢዜማ እና የግል እጩ ተወዳዳሪ)፣ ሕጋዊ ያልኾነ የምዝገባ ሒደትን የሚያሳዩ ምስሎች እና ቪዲዎችም በማኅበራዊ ሚዲያዎች ሲታዩ ነበር፤ ቦርዱም በሚዲያ ሞኒተሪንግ ክፍሉ ተሰበስቦ ቀርቦለት እነዚህን ምስሎች እና ቪዲዮዎች ተመልክቷል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...