ኅቡእ ጣት (ዘ ሀይድ)፣ አዲስ መጽሐፍ

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ሸንቁጥ አየለ

ኅቡእ ጣት (ዘ ሀይድ)
ኅቡእ ጣት (ዘ ሀይድ)፣ የሸንቁጥ አየለ አዲስ መጽሐፍ

ኅቡእ ጣት (ዘ ሀይድ) የተሰኘውን አዲሱ መጽሐፌ፤ በኢትዮጵጵያውያን፣ ኤርትራውያን እና ግብጻውያን፤ ብሎም በተጓዳኝ ያሉ አገራትን ፖለቲካዊ ስነልቦናዊ ጭብጥ፣ የፖለቲካ ኢኮኖሚያዊ ስሌት፣ አገራዊ ራዕይ፤ እንዲሁም አጠቃላይ የፖለቲካ ቀመራዊ ውል ሊፈትሽ ይባትታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"የጥፋት ዘመን" አዲስ መጽሐፍ በሙሉቀን ተስፋው

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

የመጽሐፉ ርዕስ፦ የጥፋት ዘመንYetefat Zemen by Muluken Tesfaw
ደራሲ፦ ሙሉቀን ተስፋው
የገጽ ብዛት፦ ፪፻፺፪ (292)
ዋጋ፦ ፳፭ የአሜሪካ ዶላር ($ 25)

በዓይነቱና በይዘቱ ለየት ያለ ነው። ከ1983 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 2007 ዓ.ም. በመላው ኢትዮጵያ በአማራው ህዝብ ላይ የደረሰውን ዕልቂትና የተቀነባበረ ዘር ማጥፋት ለሁለት ዓመታት በፈጀ ጥናት ተዘጋጅቶ በመላው ዓለም ለአንባቢያን ቀርቧል። ብዙ ምሁራን አስተያየታቸውን ሰጥተውበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወያኔ ለምን ”የጥፋት ዘመን” የተሰኘውን አዲስ መጽሐፍ እንዳይሸጥ አገደች?

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ሸንቁጥ አየለ

"Yetefat Zemen" new book by Muluken Tesfaw

ወያኔ ”የጥፋት ዘመን” የተሰኘውን የሙሉቀን ተስፋውን አዲስ መጽሐፍ በመላ ሀገሪቱ እንዳይሰራጭ፣ እንዳይሸጥ እና እንዳይነበብ አግዳዋለች። ግን ለምን?

ህወሓቶች እንዲህ አይነት መጽሐፍ ታትሞ ቢሰራጭ እንደሚያግዱት ገና ከጅምሩ ግምት ሳይሆን ጠንካራ ድምዳሜ ላይ ደርሼ ነበር። ይሄም የሆነው በተለያየ ወቅት ከበርካታ ወጣቶች ጋር በአማራ ህዝብ ላይ የተሰራውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በመጽሐፍ መልክ ስለማሳተም እየተወያዬን ስለነበረ እና ወያኔም መጽሐፉ ታትሞ ቢወጣ ሊያግደው እንደሚችል ሰፊ ትንታኔ ሰርተንበት ስለነበረ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ባለውለታዎችና ጀግኖቻችን የተዘከሩበት

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

የ“ኢ/ር ታደለ ብጡል የሕይወት ታሪክ አርኣያነት” መጽሐፍ የምረቃ በዓል

ተረፈ ወርቁ

ኢንጂነር ታደለ ብጡል እስከ ዛሬ ድረስ ፲፬ የሚያህሉ መጻሕፍት ለንባብ አብቅተዋል። እነዚህ መጻሕፍት በአብዛኛዎቹ ደግሞ ስለ ኢትዮጵያ ሀገራችን ታሪክ፣ አኩሪ ባህል፣ ቅርስና የቀድሞ ገናና ሥልጣኔያችንን የሚያወሱ ዘመን አይሽሬ ናቸው። ”The Origin of Humankind” የሚለው የኢትዮጵያን የሺ ዘመናት ታሪክ፣ ገናና ሥልጣኔና የህዝቦቿን ነጻነትና ልዑላዊነት በሰፊው የሚተርከው፣ በፋሽስት ኢጣሊያ ስለተወሰደውና ወደ እናት ምድሩ እንዲመልስም ከፍተኛ የኾነ አስተዋጽኦና ጥረት ስላደረጉበት የአክሱም ሀውልት፣ የዘመናዊት ኢትዮጵያ መሠረት ጣይ ስለሆነው ስለ ዐፄ ቴዎድሮስና ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ የጻፏቸው የታሪክ መጻሕፍት ይጠቀሳሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

Ethiopian Transitions: At Home and Abroad (by Kebede Haile) / የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር (ከበደ ኃይሌ)አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ

የመጽሐፉ ርዕስ፡- Ethiopian Transitions: At Home and Abroad (የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር)

ፀሐፊ፡- ከበደ ኃይሌ

ቋንቋ፡- እንግሊዝኛ እና አማርኛ

ዋጋ፡- 32.99 የአሜሪካ ዶላር (ጠንካራ ሽፋን)

የገጽ ብዛት፡- 286

አሳታሚ፡- ኦልራይት ፐብሊሺንግ

ገበያ ላይ የዋለው፡- መስከረም 14 ቀን 2008 ዓ.ም. / ኦገስት 24 ቀን 2015 (እ.ኤ.አ.)

ደራሲና ፀሐፊ ከበደ ኃይሌ በቅርቡ እንግሊዝኛ እና በአማርኛ ቋንቋ የጻፉት “Ethiopian Transitions: At Home and Abroad” (የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር) የተሰኘው መጽሐፍ በቅርቡ በገበያ ላይ መዋሉን ለኢትዮጵያ ዛሬ በላኩት ኢ-ሜይል ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ