አሳሳቢው ኮቪድ 19 በኢትዮጵያ

በበሽታው የሚያዙና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ድጋሚ እየጨመረ ነው
ከሁለት ሺሕ ሰዎች በላይ በበሽታው ሞተዋል
ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 22, 2021)፦ በኢትዮጵያ በኮቪድ 19 (ኮሮና ቫይረስ) ወረርሽኝ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ስለመምጣቱ እየታየ ነው። በበሽታው ተይዘው ከሚሞቱ ሰዎች ውስጥ የወጣቶችም ቁጥር እንደጨመረ፣ ጽኑ ታማሚዎችም ከወትሮ በተለየ ቁጥር ከፍ እያለ ነው። እስካሁን በበሽታው ተጠቅተው ሕይወታቸው ማለፉ ከተገለጹት ታዋቂ ሰዎች መካከል ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ይጠቀሳሉ። ትናንት ደግሞ የዓለም ሎሬት ጥበበ የማነብርሃን በዚሁ በሽታ ተይዘው ሕይወታቸው ማለፉን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። እንዲህ ካሉ መረጃዎች አንፃር የኮቪድ 19 በሽታ በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የሚጠቁም ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...