የኢትዮጵያ የኃይማኖት አባቶች በሊቢያ የደረሰውን ጭፍጨፋ አወገዙ
ፈረንሣይ 24 የተሰኘው የፈረንሣይ ቴሌቭዥን ጣቢያ በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ የኃይማኖት ተቋማት መሪዎች በጋራ በመሆን አይሲስ በሊቢያ በስደት በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ያደረሰውን ጭፍጨፋ ማውገዛቸውን ዘገበ። የኢትዮጵያ መንግሥት የተገደሉት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ማረጋገጡን አክሎ ዘግቧል። የሟቾችን ቤተሰቦችንም ቃለምልልስ አድርጎላቸዋል።