"የምንታገለው ሕዝባችን ዕጣ ፈንታውን በሬፈረንደም እንዲወስን ነው!" አቶ ቃሲም አባ ነሻ
የኦሮሞ ነጻ አውጭ ግንባር ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ቃሲም አባ ነሻ፤ ሰሞኑን ላስ ቬጋስ ከሚገኘው ህሊና ራዲዮ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፣ "የምንታገለው ሕዝባችን ዕጣ ፈንታውን በሬፈረንደም እንዲወስን ነው!" ከማለታቸውም ሌላ፤ ”በኦሮሚያ ያሉ ዞኖች ከፈለጉ ከኦሮሚያ የመውጣት መብት አላቸው” ሲሉ ተደምጠዋል።