የነአቶ ሀብታሙ አያሌው ጉዳይ በድጋሚ ለኅዳር ፳፯ ተቀጠረ

Habtamu, Daniel, Yeshiwas and Abrahaኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ በአራት ታዋቂ የተቃዋሚ ፓርቲ ሰዎች፤ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ አቶ አብርሃ ደስታ እና የፓርቲ አባል ባልሆኑት አቶ አብርሃም ሰለሞን የተከሰሱበትን ጉዳይ ለማየት የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ትናንት ቢሰየምም፤ የፌዴራሉ አቃቤ ሕግ በችሎቱ ባለመገኘቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእነበቀለ ገርባ ላይ የፌዴራል አቃቤ ሕግ በዝግ ችሎት ይታይልኝ ጥያቄን ፍ/ቤቱ ውድቅ አደረገው

Ene Bekele Gerbaኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ ዛሬ በዋለው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፲፰ኛ ወንጀል ችሎት፣ የፌዴራሉ አቃቤ ሕግ ትናንት የእነ አቶ በቀለ ገርባ ጉዳይ ላይ ምስክርነት የመስጠቱ ሂደት በዝግ ችሎት እንዲታይለት ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አደረገበት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቢቢሲ በሦስት የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ስርጭት ሊጀምር ነው

BBC

ኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ የብሪቲሽ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ቢቢሲ)፣ በሚቀጥለው የአውሮፓውያን አዲስ ዓመት (2017) የኢትዮጵያን ሦስት ቋንቋዎች ጨምሮ በአስራ አንድ የዓለም ቋንቋዎች አዲስ ስርጭት ሊጀምር መሆኑ ታወቀ። ኢትዮጵያውያን ቋንቋዎቹ አማርኛ፣ ኦሮምኛ እና ትግሪኛ መሆናቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ የአንድ ዓመት እስራት ተፈረደበት

Journalist Getachew Workuኢትዮጵያ ዛሬ (ማክሰኞ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 15, 2016)፦ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ፮ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ በዋለው ችሎት፤ በኢትዮ ምኅዳር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ ላይ የአንድ ዓመት እስራት እንደበየነበት ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ ጠቆመ። ጋዜጠኛ ጌታቸው ካለፈው ጥቅምት ፳፬ ቀን ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሀብታሙ አያሌውን ጨምሮ አራት ታዋቂ ፖለቲከኞች ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

Habtamu, Daniel, Yeshiwas and Abraha

ኢትዮጵያ ዛሬ (ሰኞ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 14, 2016):- አራት ታዋቂ የተቃዋሚ ፓርቲ ሰዎች፤ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ በነገው ዕለት በፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ ጠቆም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲሱ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኃይሌ ገብረሥላሴ የዕድሜ ልክ ክብር ተጎናጸፈ

Haile Geberselase

ኢትዮጵያ ዛሬ (ዓርብ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. November 11, 2016):- የዓለም አቀፉ የማራቶንና የረዥም ርቀት ማኅበር በዛሬው ዕለት ከሳምንት በፊት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፕሬዝዳንት ኹኖ የተመረጠውን አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴን የዕድሜ ልክ ሽልማት ወደር የማይገኝለት የማራቶን ሯጭ የሚል የክብር ስያሜ በመስጠት ለክብሩ የራት ግብዥ የማራቶን ውልድት ከተማ በሆነችው የግሪክ ዋና ከተማ አቴንስ አዘጋጅቶለታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነ አቶ በቀለ ገርባ ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰባቸው ለፍርድ ቤት ተናገሩ

Bekele Gerba and others- መቅረብ ከነበረባቸው 22 ሰዎች አምስቱ አልቀረቡም

- "አራቱ የተለያየ እስር ቤት ስለሆኑ አላቀረብኳቸውም አንዱ ግን የት እንዳለ አላውቅም" ፖሊስ

ከቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ በኋላ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት በአቃቤ ሕግ በሽብር ወንጀል የተከሰሱት እነ አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 22 የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አመራር አባላትና ደጋፊዎች መካከል አምስቱ ዛሬ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ ሲል የአሜሪካ ድምፅ ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዞን ዘጠኝ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ በድጋሚ ታሰረ

Zone9 blogger Befeqadu Hailu(ዞን ዘጠኝ) የዞን ዘጠኝ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ ዛሬ (ዓርብ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም./ Nov. 11, 2016) ማለዳ 12:30 ሰዓት ገደማ ኮማንድ ፓስት ይፈልግሃል በሚል ሰበብ ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ፤ እዛው መኖሪያ ቤቱ አካባቢ በሚገኝው 06 ፖሊስ ጣቢያ ታስሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዶናልድ ትራምፕ ፕሬዝዳንትነትን ከ16 ዓመት በፊት በፊልም ተተንብዮ ነበር

Screen shot of The Simpsons

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት ፴ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. November 9, 2016):- ”ዘ ሲምፕሰንስ” የተሰኘው ተከታታይ የካርቱን ፊልም እ.ኤ.አ. ሁለት ሺህ መጀመሪያ አካባቢ (ከዛሬ ፲፮/16 ዓመት በፊት) ስለዶናልድ ትራምፕ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተንብዮ ነበር። ከፊልሙ ክፍሎች ውስጥ በተለይም ”Bart To The Future” በተሰኘው ርዕስ ስለአሜሪካ ቀጣይ ፕሬዝዳንት ሽፋን ሰጥቶ እንደነበረ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን በዛሬው ዕለት ሲዘገብ ውሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ