የነአቶ ሀብታሙ አያሌው ጉዳይ በድጋሚ ለኅዳር ፳፯ ተቀጠረ
ኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ በአራት ታዋቂ የተቃዋሚ ፓርቲ ሰዎች፤ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ አቶ አብርሃ ደስታ እና የፓርቲ አባል ባልሆኑት አቶ አብርሃም ሰለሞን የተከሰሱበትን ጉዳይ ለማየት የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ትናንት ቢሰየምም፤ የፌዴራሉ አቃቤ ሕግ በችሎቱ ባለመገኘቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ።
ኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 16, 2016)፦ ዛሬ በዋለው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፲፰ኛ ወንጀል ችሎት፣ የፌዴራሉ አቃቤ ሕግ ትናንት የእነ አቶ በቀለ ገርባ ጉዳይ ላይ ምስክርነት የመስጠቱ ሂደት በዝግ ችሎት እንዲታይለት ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አደረገበት።
ኢትዮጵያ ዛሬ (ማክሰኞ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Nov. 15, 2016)፦ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ፮ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ በዋለው ችሎት፤ በኢትዮ ምኅዳር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ ላይ የአንድ ዓመት እስራት እንደበየነበት ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ ጠቆመ። ጋዜጠኛ ጌታቸው ካለፈው ጥቅምት ፳፬ ቀን ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ነበር።
አንኳር፣ ማክሰኞ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. ስርጭቱ የዕለቱን አንኳር ወሬዎች እንደሚከተለው ዘግቧል።
(ዞን ዘጠኝ) የዞን ዘጠኝ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ ዛሬ (ዓርብ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም./ Nov. 11, 2016) ማለዳ 12:30 ሰዓት ገደማ ኮማንድ ፓስት ይፈልግሃል በሚል ሰበብ ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ፤ እዛው መኖሪያ ቤቱ አካባቢ በሚገኝው 06 ፖሊስ ጣቢያ ታስሯል።



