ዲሜጥሮስ ብርቁና ተክሌ አበበ መርጋ ይከራከራሉ

Ethiopia Zare (አርብ ነሐሴ 20 ቀን 2003 ዓ.ም August 26 2011) :- ባለፈው ግንቦት የተቋቋመውና መቀመጫው በቶሮንቶ የሆነው “አድባር የክርክር ማህበር” ሶስተኛውን የክርክር ዝግጅት በያዝነው ሳምንት፡ አርብ፡ ኦገስት 26 ከሰዓት በኋላ፡ ከ5 ሰዓት ጀምሮ፡ በሂሩት የሀበሻ ሬስቶራንት እንደሚያደርግ በላከው አጭር መግለጫ አስታወቀ።

 

አድባር የክርክር ማህበር፡ ከዚህ ቀደም፡ በኢትዮጵያ ባህልና ባህላችን በፖለቲካችን ላይ ባለው ተጽእኖ፡ እንዲሁም በትዳር ግንኙነትና ጉዳዮች ላይ፡ የተሳካ ውይይት ያደረገ ሲሆን፡ በዚሕኛው ሶስተኛው ክርክር ላይ፡ ወጣት ዲሜጥሮስ ብርቁና፡ ተክሌ አበበ መርጋ፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አሁን ድረስ አከራካሪ በሆነው፡ በፖለቲካዊ ሀሳብና በብሔር የተደራጁ የፖለቲካ ሃይሎችሚያቀነቅኑት "ቅኝ ግዛት" አስተሳሰብ ላይ ይከራከራሉ።

 

ምንም አንኳን ኢትዮጵያ በታሪኳ በቅኝ ሊገዛት አስቦ ከነበረው የኢጣሊያን ወራሪ ሃይል ጋር መራር የሆነ ትግል በማድረግ ነጻነቷን በማስጠበቋ ለብዙ ጥቁር ህዝቦች የመንፈስ ብርታት አና ኩራት ብትሆንም፤ 1960ዎቹ ብቅ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ግን ኢትዮጵያ የቅኝ ገዢ ሃገር ናት፡ የሚል የፖለቲካ ሃሳብ ያቀነቅናሉ። ለዚህም እነደ ሕወሀት፡ ሻእቢያ፡ ኦነግ አና የኦጋዴን ነጻ-አውጭ ግንባር ያሉ ይሄንን “ኢትዮጵያ ቅኝ ገዢ ናት”” ሃሳብ በማቀንቀን ይታወቃሉ። ይሄ ስህተት ነው የሚለው ዲሜጥሮስና፡ የለም “ኢትዮጵያ ቅኝ ገዢ ናት ባንልም፡ ከዚያ ባነሰ መልኩ ግን ከሁለት መቶ አመታት በላይ ነጻ የነበሩ ራሳቸውን የቻሉ ግዛቶችን በጉልበት ይዛለች” ከሚለው ልጅ ተክሌ ጋር ይከራከራሉ።  

 

ለመሆኑ ኢትዮጵያን በቅኝ ገዢነት ሊያስከስስ የሚችል ምን ታሪካዊ መሰረት አለ? ምሁራን አና ተመራማሪዎችስ ለጉዳዮ ድጋፍ ኣላቸው ወይ? ካለ በምን በምን ምክንያት? ተክሌ አበበ አና ድሜጥሮስ ብርቁ በፈረንጆቹ አቆጣጠር ኦገስት 26,2011 ተቃራኒ ጎኖችን ይዘው በቶሮንቶ ክርክር ስለሚያደርጉ፡  በቶሮነ አና ኣካባቢው ያላችሁ ኢትዮጵያውያን በሂሩት ሬስቶራንት (አድራሻ-2050 ዳንፎርዝ አቬኒዮ ፤ቶሮንቶ) በቶሮንቶ አና አካባቢዉ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን እንድትገኙ ጋብዘዋል።

 

ክርክሩ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች መወያያ መድረክና በቃሌ፡ እንዲሁም በሌሎች የፓልቶክ ክፍሎችም ስለሚተላለፍ፡ በፓልቶኮች እንድትከታተሉ ግብዣ ቀርቧል። አድባር ከዚህ በፊት ያደረጋቸውን ክርክሮች ዝርዝር ዘገባ፡ እዚህ ላይ ይመልከቱ። http://www.facebook.com/groups/218520534848685/

 

ወጣት ተክሌ፡ ከቶሮንቶ፡ ካናዳ፤ ነሀሴ፡ 2011

 

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ