አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ላልተወሰነ ጊዜ መዘጋቱ ተገለጸ
ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 26, 2020)፦ አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካን ኤምባሲ ከኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ጋር በተያያዘ ላልተወሰነ ጊዜ የኤምባሲ አገልግሎት እንደማይሠጥና እንደተዘጋ አስታውቋል።
ኤምባሲው ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2012 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፤ ከቫይረሱ ሥርጭትና የኢትዮጵያ መንግሥት ከሚያደርገው ጥረት ጋር ተያይዞ ኤምባሲውን ላልተወሰነ ጊዜ መዝጋቱን አስታውቋል። (ኢዛ)