Office of the Prime Minister, Ethiopia

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

የወንጌላውያን ካውንስል ሕጋዊነትን የሚያረጋግጥ አዋጅ ይጽደቅ ብሏል
የልማት ባንክን የማቋቋሚያ ስዋጅ እንዲሻሻል ወስኗል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 7, 2020)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. ባካሔደው ሃያኛው አስቸኳይ ስብሰባ የኢትዮጵያ ልማት ባንክን ማቋቋሚያ ደንብ እንዲሻሻል ውሳኔ ሲያሳልፍ፤ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ሕጋዊ ሰውነት ለመስጠት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ እንዲጸድቅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቷል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ስብሰባው ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈባቸው ሌሎች ጉዳዮች ደግሞ፤ የብሔራዊ ትርናፖርት ፖሊሲ እና የሎጅስቲክ ፖሊሲዎች ይገኙበታል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች በተመለከት የተሰጠው መግለጫ የሚከተለው ነው። (ኢዛ)

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ