ገ/ኢ. ጐርፉ

በውድቅት ሌሊቱ

ከሞቀው አልጋዬ

በወቅቱ፣ በሰዓቱ

ብርድ-ልብስ ደርቤ

ተከናንቤ

ሃሳቤ እሹሩሩ ...

ብቻውን ነጐደ!

ያላበው ገላዬ

በቅዠት አበደ

እንቅልፍ እንጅሩ!

ስወራጭ፣ ሳልተኛ፣

ስገላበጥ ክፉኛ

አጉል ነጋብኛ ...

እንቅልፍ የት አባቱ

ሄደ …

ቢሮ ገብቼ ግን ሥራ ሲያፋጥጠኝ

ወይ ስቃዬ!

ሳልሞት፣ በውኔ

ቁጭ ብዬ ወንበር ላይ

ፍዝዝ ይላል ዓይኔ

አለቃዬ

ዓይን-ዓይኔን ሲያይ

ወይኔ፣ ወይኔ!

ነቅቶ መቀመጡ

እምቢዮ ይለኛል

ዓይኔን መግለጡ …

ያቅተኛል

ሽልብ ያደርገኛል …

ምን አባቱ!

ገ/ኢ. ጐርፉ

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ