አገርና እንጀራ / መቶ ሲደመር አንድ/
/ደመቀ ከበደ - ዓባይ ዳር/

ይቺ አገር - የኛ አገር
አንዴ ´ምትቦካ - አንዴ ´ምትጋገር፤
ሲሻ ´ምትወድቅ - ሲሻ ´ምትሻገር
አንዴ ባንተ ነበር - አንዴም በኛ ነበር፤

አገር እንደ ተረት - ‹‹ተረት›› ከተባለ
ተረት ነው አገርህ - በል ተርት ምናለ፤
አገር እንቆቅልሽ - ይሁን ከተባለ
‹‹እንቆቅልሽ አገር›› - ይኸውልህ አለ፤
አገር እንደ ፈሊጥ - ምሳሌ ከሆነ
ከኛዋ አገር በላይ - ምንም ‹‹ፈሊጥ›› የለ፤

አንዱ ‹ሲተርታት› - እሳት ዳር ቁጭ ብሎ
አንዱ ይሰማዋል - ‹‹የመሰረት›› ብሎ፤
ሌላው ‹እንቆቅልሽ› - ሲያደርጋት ጨክኖ
‹ምን አውቅልህ?› ይላል - ያኛው ከጎን ሁኖ፤
ቀሪው እንደ ‹ፈሊጥ› - ቃል ሲያሳምርባት
ይኸ በምሳሌው - አለ ሲስቅባት፡፡

ይቺ አገር - የኔ አገር
ይቺ አገር - የአንተ አገር
ይቺ አገር - የአንቺ አገር
ይቺ አገር - የኛ አገር / የሁላችን አገር /
አንዴ ስትቦካ - አንዴ ስትጋገር፤
በአቡኪና ጋጋሪ - ልኳ እየተለካ
ቀድሞ ባልተፈጨ - ሊጧ እየተቦካ
አለች እስከዛሬ - ሳትመር ሳትጥም
መጋገሪያው ምጣድ - ከሙግዱ ሳይገጥም፡፡

ለዚያም ነው
የዚያኛውን አቡኪ - ይኸ እየጋገረው
ያ የጋገረውን - አንዱ እየሰበረው
በሰባራ ምጣድ - እንደ እንኩሮ እንጀራ
በመጣ፤ በሄደ - አገሬ ተጋግራ
ይህንን እንጀራ
የመጣ ጋጋሪ - ወይም ባለተራ
ለባለ አገር ሁላ - ቢያበላ፣ ቢያበላ
ጠኔ አላጠገገም - ራብም አልከላ!

ምክንያት፤
የአያቶቹን ምጣድ - አባት እየሰበረ
የአባቶቹን ምጣድ - ልጅ እየቀየረ
አገር እያቦካ - ቀዬ እየጋገረ
እልፍኝ እያበጀ - ከልካይ እያኖረ
አብሲቱን ህዝብ ግን - ይረሳው ነበረ፤

እና እንዲህ እላለሁ፤
ማነህ ባለተራ?
ምጣድ ያዘጋጀህ - ለእንጀራ ጋገራ?!
እሳት ዳር ቁጭ ብሎ - ፍሙን እየሞቀ
ከትላንት ጥጥ ላይ - የታሪክ ባዘቶ - እየፈለቀቀ
እያጠነጠነ - ሸማ እያጠለቀ
ህዝብ ይኑርልኝ ካልክ - እየፈነደቀ
በሰባራ ምጣድ - ሊጥ አታነካካ
ባለፈው ጋጋሪም - ሙያህን አትለካ
ይልቅ የእልፍኙን ሰው - ሌማቱ እንዲያረካ
በአገር ልክ ጋግር - ከህዝብ ጋር አቡካ!!
Photo: አገርና እንጀራ / መቶ ሲደመር አንድ///ደመቀ ከበደ - ዓባይ ዳር//ይቺ አገር - የኛ አገርአንዴ ´ምትቦካ - አንዴ ´ምትጋገር፤ሲሻ ´ምትወድቅ - ሲሻ ´ምትሻገርአንዴ ባንተ ነበር - አንዴም በኛ ነበር፤አገር እንደ ተረት - ‹‹ተረት›› ከተባለተረት ነው አገርህ - በል ተርት ምናለ፤አገር እንቆቅልሽ - ይሁን ከተባለ‹‹እንቆቅልሽ አገር›› - ይኸውልህ አለ፤አገር እንደ ፈሊጥ - ምሳሌ ከሆነከኛዋ አገር በላይ - ምንም ‹‹ፈሊጥ›› የለ፤አንዱ ‹ሲተርታት› - እሳት ዳር ቁጭ ብሎአንዱ ይሰማዋል - ‹‹የመሰረት›› ብሎ፤ሌላው ‹እንቆቅልሽ› - ሲያደርጋት ጨክኖ ‹ምን አውቅልህ?› ይላል - ያኛው ከጎን ሁኖ፤ቀሪው እንደ ‹ፈሊጥ› - ቃል ሲያሳምርባትይኸ በምሳሌው - አለ ሲስቅባት፡፡ይቺ አገር - የኔ አገርይቺ አገር - የአንተ አገርይቺ አገር - የአንቺ አገርይቺ አገር - የኛ አገር / የሁላችን አገር /አንዴ ስትቦካ - አንዴ ስትጋገር፤በአቡኪና ጋጋሪ - ልኳ እየተለካቀድሞ ባልተፈጨ - ሊጧ እየተቦካአለች እስከዛሬ - ሳትመር ሳትጥምመጋገሪያው ምጣድ - ከሙግዱ ሳይገጥም፡፡ለዚያም ነውየዚያኛውን አቡኪ - ይኸ እየጋገረውያ የጋገረውን - አንዱ እየሰበረውበሰባራ ምጣድ - እንደ እንኩሮ እንጀራበመጣ፤ በሄደ - አገሬ ተጋግራይህንን እንጀራየመጣ ጋጋሪ - ወይም ባለተራለባለ አገር ሁላ - ቢያበላ፣ ቢያበላጠኔ አላጠገገም - ራብም አልከላ!ምክንያት፤የአያቶቹን ምጣድ - አባት እየሰበረየአባቶቹን ምጣድ - ልጅ እየቀየረአገር እያቦካ - ቀዬ እየጋገረእልፍኝ እያበጀ - ከልካይ እያኖረአብሲቱን ህዝብ ግን - ይረሳው ነበረ፤እና እንዲህ እላለሁ፤ማነህ ባለተራ?ምጣድ ያዘጋጀህ - ለእንጀራ ጋገራ?!እሳት ዳር ቁጭ ብሎ - ፍሙን እየሞቀከትላንት ጥጥ ላይ - የታሪክ ባዘቶ - እየፈለቀቀእያጠነጠነ - ሸማ እያጠለቀህዝብ ይኑርልኝ ካልክ - እየፈነደቀበሰባራ ምጣድ - ሊጥ አታነካካባለፈው ጋጋሪም - ሙያህን አትለካይልቅ የእልፍኙን ሰው - ሌማቱ እንዲያረካበአገር ልክ ጋግር - ከህዝብ ጋር አቡካ!!

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ