የረቡዕ ግጥም ፪ኛ ዓመት፣ ፶፪

ይቺ መዝጊያ ትሁን

መቶ አራት ግጥሞችን ተሸክሜ ይዤ

ረቡዕ ረቡዕ ስጥል አንድ አንዷን መዝዤ

በዚች በአሁኗ ቀን በጨበጥናት ሳምንት

ወሩን ስደምረው ሆነኝ ሁለት ዓመት

ዳግም በአዲስ ዓመት እስከምንገናኝ

የዘንድሮው መዝጊያ ይቺ ትሁንልኝ

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዱባም አይቦዝንም (ክንፈሚካኤል ገረሱ)

ክንፈሚካኤል ገረሱ

ጊዜን እያሰሉ በሰዓት መጥኖ፣
በጥበብ በምጥቀት ዓላማን ከውኖ።
ትላንትናን ሳይሆን ዛሬን እየኖሩ፣
የሕይወትን ቅኔ እየመሰጠሩ።
እንደ ጧፍ ተቃጥሎ እንደ ሰምም ፈሶ፣
ለተተኪው ትውልድ አሻራን አውርሶ።
ይህ ነው መኖር ማለት መመላለስ በዓለም፣
እንደ ሻማ ቀልጦ የአዳም ዘርን መጥቀም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሸረበው ጅራፍ (ክንፈሚካኤል ገረሱ)

ክንፈሚካኤል ገረሱ

ከዕለታት አንድ ቀን ስድስት ሰዓት ግድም፣
ገሚሱ ሲያሻቅብ ገሚሱ ሲያገድም።
አለቃ ደክሟቸው ወደ ቤት ሲያዘግሙ፣
አመሻሽ አዳሩን ሲቃኙ ሲያልሙ።
በሃሳብ ጅረት ባህር ሲቀዝፉ ሲዋኙ፣
ካንድ ከሚያውቁት ሰው ድንገት ተገናኙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ