ፍርሃትን ስፈራው (ክንፈሚካኤል ገረሱ)
እኔ!
አንበሳ እፈራለሁ፣
በዘንዶ እርዳለሁ።
እኔ!
አንበሳ እፈራለሁ፣
በዘንዶ እርዳለሁ።
ክንፈሚካኤል ገረሱ
ከወዳጅ ቢጣሉ ፈጥነው ይታረቋል፣
ጎረቤት ቢከፋ ሰፈር ይለቀቃል።
ደዌ ቢያጠቃዎት ይሽራል በሐኪም፣
ፈተና ቢበዛ ያልፋል እንደምንም።
ውድቀት ቢያጥለቀልቅ ይሳካል በሂደት፣
አመል ቢነሳዎት ይቃናል በትግስት።
ከዛፍ ላይ ስትቀልስ አሞራ ቢያፈርሰው፣
ከካብ ስር ስትሠራ እባቡ ቢንደው።
ሜዳ ላይ ስታንፅ እረኛው ቢገዳት፣
”የት ውዬ የት ልደር” አለች ቢቸግራት።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ወተት ባይኔ ዞሮ አምሮኝ ውል ብሎኝ፣
ወጥቼ ወርጄ ’ርጎ ብጤ ባገኝ።
ሳልቀምስ ሳልጠጣው ቀልቤ ሲስገበገብ፣
ገብታ ዋኘችበት አታፍር የ’ርጎ ዝንብ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ክንፈሚካኤል ገረሱ
ዓይንና አፍንጫዬ ተጋጭተው አንድ ቀን፣
ሲንቅ ሲያንኳስሰው አንዱ ሌላኛውን።
ነገሩ ቢደንቀው ጆሮ አሽሟጠጣቸው፣
ጥርስ ሳቀባቸው ምላስ ታዘባቸው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...