“ካፊርስ አንተ ነህ” (ዳዊት ከበደ ወየሳ)
ይሄ የምታዩት፣ ካገሩ የወጣ፣ ኮበላ እና ጉብል፤
ቢሆንበት እንጂ፣ ነገሩ አጓጉል፣ ወጥቶ ‘ሚኮበልል።
ባህሩን በታንኳ፣ በርሃውን በ’ግሩ፣ ምድሩን በመኪና፤
ያልፍልኛል ብሎ፣ ድንበሩን ሲሻገር፣ ሰው አገር ሲያቀና።
መች ጠልቶ አገሩን፣ መች ከድቶ ወገኑን፣ መች ሻረ ማተሙን፤
በክርስትና ስም፣ እንደመዳኒአለም፣ አፈሰሰ ደሙን።
ሙሉውን አስነብበኝ ...




