መቆጣት ያቃተው ወይስ … ህዝብ (ዳናቸው ቢያድግልኝ)
መቆጣት ያቃተው ወይስ ቁጣውን ወደ ተግባር መለወጥ የተሳነው ህዝብ
ዳኛቸው ቢያድግልኝ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
በሀገራችን የተለመደው በደስታም ይሁን በኀዘን አብሮነት ነበር። እኒህ የፎቶ መረጃዎች ግን የሚያመለክቱት አስተዛዛኝም ጭምር የጠፋበትና ልጅን በብርድልብስ ጠቅልሎ ብቻውን ወደ ቀብር መሄድን ነው። ይህ ዝነኛውና አረንጓዴው ረሃብ በመባል የሚታወቀውና በተለይ በደቡብ ክልል ያለውን ህዝብ እያጠፋ ያለው ምርት አልባነት ነው። በለምለሙ መስክ ላይ የእህል ክምር ሳይሆን የሕፃናት ሬሳ የሚቆለልበት የሀገራችን ክፍል መሆኑ ነው።
ልጆቹን በቀረችው ብርድልብስ ገንዞ ብቻውን የሚቀብር ህዝብ ነው የትግራይ ልጆችን ለማስተማር ይሆን ዘንድ ለትምህርት ቤታቸው ማሰሪያ ገንዘብ የሚያበረክተው። የትግራይ ልጆች ሲማሩ የደቡብ ሕፃናት በረሃብ እየረገፉ ለዐረብ ቱጃር ለሚሸጡ መሬቶች ማዳበሪያ ይሆናሉ።