በጎንደር የሱዳኖችን ጥቃት በተመለከተ (ግርማ ካሣ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Atsé Yohanesግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

(ሚያዝያ 24 ቀን 2000 ዓ.ም. May 2, 2008)

“ዐፄ ዮሐንስ ይዋሻሉ

መጠጥ አልጠጣም ይላሉ

ሲጠጡ አየናቸው በርግጥ

እራስ የሚያዞር መጠጥ”

 

ይህ ለዐፄ ዮሐንስ አራተኛ የተገጠመ ቅኔ ነበር። ሰሙ፣ ዐፄ ዮሐንስ መጠጥ አልጠጣም እያሉ የሚያሰክር መጠጥ ሲጠጡ እንደሚታዩ የሚገልጽ ሲሆን፤ የቅኔው ዋና መልዕክት - ወርቁ ግን የእኝህን ታላቅ ኢትዮጵያዊ የደም መስዋዕትነት ያሳያል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"የሞራል እኩልነት ጥያቄዎችና የአመለካከት ችግራቸው" ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ቅዳሜ ሚያዝያ 11 ቀን 2000 ዓ.ም. (አፕሪል 19 ቀን 2008 እ.ኤ.አ.) በቶሮንቶ ከተማ ካናዳ ከኢትዮጵያውያኖች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ "የሞራል እኩልነት ጥያቄዎችና የአመለካከት ችግራቸው፤ ምን ያህሉ ከተግባር ለመራቅ የሚደረግ እራስን የመሸንገያ መሣሪያ ነው?" በሚል ርዕስ ንግግር አድርገዋል። ሙሉ ንግግሩን በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ። (Read on PDF)


አፍሪካና ምርጫ (ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

Prof. Mesfin Woldemariamመስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር) - ሚያዝያ 2000

ምርጫ የነፃ ሕዝቦች መግለጫ ነው፤ ነፃ ሕዝቦች የአገራቸውንና የመንግሥታቸው ባለቤቶች ናቸው፤ ስለዚህም ምርጫ የአገራቸውና የመንግሥታቸው ባለቤትነታቸውን የሚያረጋግጡበት ዘዴ ነው። በአንፃሩ ደግሞ ነፃ ላልሆኑ ሕዝቦች ምርጫ ለሕዝቡ ፋይዳ የሌለውና የገዢዎቹን ጅራፍ ለመጎንጎኛ የሚያገለግል እጅ መንሻ ነው፤ በአፍሪካ ምርጫ የሚባለው የሁለተኛው ዓይነት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፍትህ ማሽቆልቆል ጉዞ በኢትዮጵያ (ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም)

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ከዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማሪያም

1. መነሻው

አንድ ማኅበረሰብ እንደ ማኅበረሰብነቱ እንዲቀጥል ከተፈለገ በረቀቀ መልኩም ይሁን በግርድፉ የህዝብ መስተጋብሮችን የሚያስተናግዱ፣ የሥራ ኃላፊነትንና ድርሻን የሚያደላድሉ፣ መሠረታዊ ፍላጎቶችን የሚያሟሉ ሕጎች መኖር የግድ ይላል። በመሆኑም እንደ አንዳንድ ጥንታዊ የዳበረ ኅብረተሰብ ኢትዮጵያዊያን ያለ ሕግ የኖሩበት ጊዜ የለም ማለት ይቻላል። ከዚያም አልፎ ዛሬ ሕጎቻቸው ዳብረው፣ ፍትሕ ሰፍኖባቸው፣ ህዝቡ መብቱ ተከብሮለት፣ ነፃነቱ ተጠብቆለት የምናያቸው ብዙዎቹ የዓለም መንግሥታት ባልተፈጠሩበት ዘመን በኢትዮጵያ በጽሑፍ የሰፈሩ የህዝቡን መስተጋብር የሚያስተናግዱ፣ የነገሥታቱና የባላባቱ ሥልጣን ስፋትና ወርድ ዳር ድንበሩን የሚከልሉ፣ በዳይን የሚወቅሱ፣ ተበዳይን የሚክሱ ሕግጋት ነበሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዳንኤልና ነፃነት (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

Prof. Mesfin Woldemariamከፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም - መጋቢት 2000

በጥቅምት 1998 ዓ.ም. ላይ የሚያዝያ 1997 ዓ.ም. የህዝብ ስብሰባ እና ተከታትሎ የመጣው ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነት ያለውን ቁርጠኛ ፍላጎት አሳየ፤ ተደላድለው የነበሩ ወንበሮችን አነቃነቀ፤ በትምክህት አብጠው የነበሩትን ሁሉ ልባቸውን በፍርሃት አርበደበደው፤ ከታች መሰረት፣ ከጎን ምሰሶ፣ ከላይ ጣሪያ የሌላቸው መሆናቸውን ያለጥርጥር እንዲገነዘቡ አደረጋቸው፤ ጭካኔ ከፍርሃት ተለወደ። የፍርሃት ልጅ ያስከተለው መዘዝ ወዳጅንና ጠላትን የመለየት ችሎታችንም እስከመንሳት ደረሰ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...