“ካርቱም ሄዶ ቀረ” እንዲሁም “ካምፓላ ሄዶ ተቀረቀረ”

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ክፍሉ ሁሴን

ስደት ለወሬ ያመቻል እንዲሉ በ1999 ዓ.ም ስደት ከገባሁ ጀምሮ መጽሐፍ እጽፋለሁ እያልኩ እንደፎከርሁ አለሁ። ሳልሞክር ግን አልቀረሁም። በተለያየ ጊዜና በተደጋጋሚ እያነሳሁ ከጣልኩ በኋላ ለስንፍናዬ መጽናኛ ያደረኩት በቅርቡ እስተወዲያኛው ያሸለበው ስብሃት ገብረእግዚያብሄር በአንድ ወቅት በራዲዮ ቃለምልልስ “ከመጻፍ መኖር ይበልጣል፤ የምንጽፈው ከኑሮ ነውና” ያለውን በመውሰድ ‘መች ኖርኩና ለመጻፍ እጋበዛለሁ’ ብዬ ራሴን ቀስ በቀስ በቁመና እየገዘገዝኩት እገኛለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሳዛኙ ዜና ኀዘን

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ወለላዬ ከስዊድን This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

መቼም ተስፋዬ ገብረአብ ከጻፈ አንድ ትዝታ የሚጭር ወይም ስሜት የሚነካ ነገር አያጣም። ባለፈው ሣምንት ”አሳዛኝ ዜና” በሚል ርዕስ በጻፈው ጽሁፉ ደግሞ ስሜቴን መንካት ሳይሆን በክፉ የኀዘን ትዝታ ውስጥ ዘፍቆኝ ሰነበትኩ። እንዴት ሆኖ ማለትዎ አይቀርም፤ እነሆ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሐበሻ በየመን - ክፍል 6 (ግሩም ተ/ኃይማኖት)

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ግሩም ተ/ኃይማኖት

ሐበሻ በየመን

ይህን ጽሑፍ በመጽሐፍ መልክ ካዘጋጀሁት ላይ ቦጨቅ ድርጌ ለማስነበብ የወደድኩት ወድጄን አይደለም። አቅሙ ኖሮኝ መጽሐፉን እስከ አሳትመው ድረስ በስደት ከሚያልቁ ወገኖቼ አንድም ሁለትም ከሞት ማዳን ከቻልኩ ብዬ ነው። በሶማሊያ እና በጅቡቲ አድርገው ወደ የመን ሲሻገሩ ባህር ላይ በአመት የሚያልቁትን ከ2000 በላይ ወገን ቁጥር በአንድም ቢሆን መቀነስ ያስደስታል። ያ-ነውና አላማዬ እባክዎትን ስደት ... በተለይ ወደ የመን፣ ሳዑዲ ... በባህር ለመጓዝ ላሰቡ ሰዎች ከመንገር አልፈው ቪዲዮውን ያሳዩልኝ። አንድ ወገን ለማትረፍ እንረባረብ የዛሬ መልዕክቴ ነው። አሁን ወደ ቀጣዩ ጽሑፍ እናምራ …

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሐበሻ በየመን - ክፍል 5 (ግሩም ተ/ኃይማኖት)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ክፍል 5

ግሩም ተ/ኃይማኖት

Sedet

ማንም የዳስሰው አይመስለኝም። የቀይ ባህር እና ህንድ ውቅያኖስ መጋጠሚያ Gulf of aden አሰቃቂ ጉዞ እና የሱማሊያውያኑን ኢሰብአዊ ድርጊት፣ የእኛም በጉዞ ላይ የዘቀጠ ማንነት.የሚካተትበት ትረካ ነው። መሳፈሪያው ቦታ እስክንደርስ እና ለመሳፈር ባህሩ ጋር ስላለው ነገር ያለውን እንዝለለው። አሁን ምናቦትን አውሱኝ እና የትራንስፖርት ሳይከፍሉ እንጓዝ … ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሐበሻ በየመን - ክፍል 4 (ግሩም ተ/ኃይማኖት)

የአንባብያን ድምፅ: 2 / 5

Star ActiveStar ActiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ክፍል 4

ግሩም ተ/ኃይማኖት

ሰናይት ካቀረቀረችበት ቀና ማለት አሳፈራት ... ልጁ ደግሞ ደግሞ ቢያናግራትም … ቀስ ብዬ አቀፍኳት እና ”... ይህ የህይወት ሂደት ነው መውደቅ መነሳት አለ። ግን ለምን ሰኒ ልጅሽስ? ባልሽስ? እነሱን ጥለሽ ይህ አይነት ህይወት ይሻላል? ለምን ወደ ሀገር አትመለሽም? ...” ብዙ ብዙ ነገር አልኳት። ልጁ አየኝ እና ”እ … ቢዝነስ አግኝተሻል? በቃ አልማዝ ስሪ ...” አለ። ሰናይት ባህሩን ለመሻገሪያ ብቻ አማራጭ አጥታ እንደምትሰራ ነገረችኝ። ”ሳዑዲ ናት የተባለወውስ?። አልኳት። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሐበሻ በየመን - ክፍል 3 (ግሩም ተ/ኃይማኖት)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ያሳዝናል…ከማለት ጀምሮ የሰነዘራችሁት ብዙ..ብዙ አስተያየት ገነቢ ነው ተቀብያለሁ። ይገባኛል። በክፍል ሁለቱ ታሪክ ብዙዎቻችሁ ማዘናችሁ ደስ ብሎኛል።  ሀዘኔን የሚጋራኝ በማግኘቴ እንጂ የሰው ስቃይ የሚያስደስተው ሳዲስት ሆኜ አይደለም ማዘናችሁ ደስ ያለኝ። እንዲያውም እኔ ላይ በደረሰው ሳይሆን ሰዎች ላይ የደረሰ ግፍ እና እልቂት በማየቴ በሀዘን፣ በጭንቀት.. በመንፈስ ጭንቀት ታምሜ የመን ያሉ ወገኖቼ አሳክመው አድነውኛል፡፡ ለዚህ ህዝቡ ምስክር ነው። በየቦታው የተሰነዘረው አስተያየት ይህ መፅሐፌን ተሳክቶልኝ ባሳትመው ምን ያህል መልዕክቱ ሊያስተምር፣ ሊያሳዝን፣ ወገን ለወገኑ እንዲያስብ ሊያደርግ..ይችልላል? የሚለውን እንዳስብ አድረጋችሁኛል። አመሰግናለ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ