ደስታዬን ማመቅ አልቻልኩም

አንዱዓለም ተፈራ - የእስከመቼ አዘጋጅ
ያለንበትን ወቅት ማመን አስቸግሮኛል። ከጥቂት ቀናት በፊት የነበረኝ ግንዛቤ፤ ጠቅልሎ ከኔ ጠፋ። ፍጹም ያልጠበቅሁት ክንውን፤ ገሃድ ሆኖ፤ አይደረግም ያልኩት ተፈጽሞ፤ የአገራችን የፖለቲካ ሐቅ ተገለባብጦ ሳገኘው፤ ሰውነቴን ዳሰስኩ። የፈለግሁት ሆነ! ብል ስሕተት ነው። ነገር ግን፤ እየተደረገ ባለው ሂደት ያለሁበትን ማመን አቅቶኛል። ደስ ብሎኛል። ሂደቱ መቀጠል አለበት እላለሁ። ደስታዬን ግን ለራሴ አፍኜ መያዝ አልፈልግም። ለዚህም እንኳን ለዚች ቀን እላለሁ። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ድፍረትና ብሩህ ገጽታ አደንቃለሁ። አገራችን አሁን ባለችበት የፖለቲካ ሁኔታ መቀመጥ ነበረባት ወይ? አለባት ወይ? በፍጹም!
ሙሉውን አስነብበኝ ...