የወያኔ ኑዛዜ፣ ከደደቢት እስከቤተ መንግሥት
(በወያኔአዊ ቋንቋ የተጣፈ ስላቅ)
ዘጌርሳም
ከደደቢት በመነሳት አራት ኪሎ ለመድረስ ረጅምና አድካሚውን ጉዞ የጀመርነው ገና ጎሕ ሳይቀድ ነበር። ከፊት ለፊታችን የተንጣለለ የአርብቶና አርሶ አደር ልማታዊ እንቅስቃሴ ይካሄዳል። እንስሳቶች ሳይቀሩ ደፋ ቀና ይላሉ። ልማታዊውና አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊው መንግሥት በመልሶ መደራጀት ያሰባሰባቸው ናቸው። አብዛኞቹ ተጋዳሊቶችና ተጋዳዮች ሲሆኑ፤ በተለጣፊነት የተሰለፉም አሉበት። ተለጣፊዎቹ በአብላጫ የሚያገለግሉት በእቃ ተሸካሚነትና መንገድ መሪነት ሲሆን፣ ፈንጂ እንዲመክኑም ይታዘዛሉ። ተለጣፊዎቹ በአብላጫው ከአናሳ ብሔረሰቦች የመጡ ሲሆኑ፣ የተማረኩና የጥቅማጥቅም ተስፋ የተሰጣቸው፣ ከትምክህተኞችና ጠባብ ብሔረተኞች የመጡ በቁጥር ብዝኀትነት አላቸው። ሕጉ አሁንም በረሃ ላይ እንደነበረው ስለሆነ ዕንስታትና ተባዕታት አብረው እንዲታዩ ቅቡልነት የለውም። ይህ ተጥሶ ቢገኝ ወደ ባዶ ስድስት ያስወረውራል። በአንፃራት ግን ዕንስት ከዕንስት፣ ተባዕት ከተባዕት መገናኘት ትግሉን ለመሸርሸር እስካልተንቀሳቀሱ ድረስ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ መብታቸው ነው። እነሱም ቢሆን ይህ በሕገመንግሥቱ ቅቡልነቱ ታውቆ እንደተረጋገጠ ያውቃሉ። ጉዳዩን አስመልክቶም የትሃድሶ ሥልጠና በየደረጃውና ዘርፉ ተሰጥቷል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...




