በወያኔ ዘመን ቀልዶች ለአፍታ ፈገግ በሉ!
ዳግማዊ ጉዱ ካሣ (ከአዲስ አበባ)

አንጀት እያረረ እርሱ ስለሚስቅ ሊሆን ይችላል “ጥርስ ሞኝ ነው” ይባላል - እንደማሽላዋ። ቢሆንም አይብዛ እንጂ ቁም ነገርን እያዋዙ በቀልድ መሰል እውነተኛ ገጠመኞች ማስተላለፍ መጥፎ አይደለም። አንድ ስዕል በሺህ ቃላት ይመነዘራል እንደሚባል አንድ ቀልድም በአንድ መጽሐፍ ቢመነዘር ቀልዱ ከሚሸከመው ቁም ነገር አንጻር ቢያንስ እንጂ አይበዛበትም። እናም ዛሬ የማስኮመኩማችሁ የወያኔ ዘመን ቀልድ በጣም ሊያስቃችሁ ስለሚችል ለዐይን ማበሻ መሐረብ ወይም እራፊ ጨርቅ ይዛችሁ አንብቡ። ትግሬ የሆናችሁ ወገኖቼ ከዘረኝነት ፈንጣጣ ካልተሸለማችሁና እንደጤነኛ ሰው ማሰብ ካልቻላችሁ በስተቀር ልትናደዱና ልትቆጡ ትችሉ ይሆናል። መፍትሔው ታዲያ አለማንበብ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...








